Quantcast
Channel: የቫቲካን ሬድዮ
Viewing all 1660 articles
Browse latest View live

2ኛ ሰንበት ዘአስተምህሮ - ሎቱ ስብሓት ወአኰቴት

$
0
0

«...በቅዱሳንም ርስት በብርሃን እንድንካፈል ያበቃንን አብን እያመሰገናችሁ በነገር ሁሉ ደስ ልታሰኙ ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን…እርሱ ከጨለማ ስልጣን አዳነን፣ወደሚወደው ልጁ መንግስትም አሻገረን፡፡» (ቆላስይስ 1፡12-14 )

በዚህ በሐዋርያው መልዕክት አማካኝነት ስለተሰጠን እና ስለተቀበልነው፣እንዲሁም አሁን ሆነን ስላለነው ሁሉ እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ ተጋብዘናል፡፡ ሐዋርያው እግዚአብሔርን ከምናመሰግንበት ምክንያቶች ዋና ዋናዎቹን እንዲህ ያስቀምጣቸዋል፡- የቅዱሳን ርስት ተካፋዮች ስደረገን፣የጻድቃን ጉባዔ አባላት እንድንሆን ስለመረጠንና ከነሱም ጋር ስለቆጠረን፣ከጨለማ ግዛት ነጥቆ ስላወጣን፣በውድ ልጁ ደም ስለዋጀንና የኃጢአትን ይቅርታ ስላገኘን፣ሁሉን ውብ ማደረግ ስለሚችል ስላደረገና ውብም እያደረገ ስለሆነ፣ወደ ዘለዓለማዊው መንግስት ስላሻገረን ወዘተ፡፡ ስለነዚህና ቁጥራቸው ስለበዛ ስጦታዎቹና በረከቶቹ እግዚአብሔርን ማመስገን የአማኝ ባህሪ ነው፡፡ ይህን ሁሉ ስጦታ እና ሌሎችንም የተቀበለ ክርስቲያን ቃለ እግዚአብሔር እንደሚለው በሰጪው ፊት ምንም እንዳለተቀበለ ባዶ እጁን ይቀርብ ዘንድ ተገቢ አይደለም (ኦ. ዘዳ. 16፡16 ተመ.)፡፡

የእግዚአብሔር ዓላማ የእጁ ስራ የሆነው ሰው ከዘለዓለማዊ ሞት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት እንዲሻገር ስለሆነ ዛሬ በተሰጠን ዕድልና ፀጋ ተጠቅመንና ሰርተንበት ሰማያዊ ቤታችንን፣ዘለዓለማዊ ማረፊያችንን እናዘጋጅ፣ከጨለማ አስተሳሰባችን እና ከጠማማ መንገዳችን ወጥተን ለእግዚአብሔር እንለይ፤ እግዚአብሔር በልጁ መስዋዕትነት ለያንዳንዳችን መዳን ዋጋ ከፍሏል፣በልጁ ደም ከእኛ ጋር ቃል ኪዳን ገብቷል፡፡ ስለዚህ ከእኛ የሚጠበቀው በውስጣዊ መታደስና በንስሐ ወደርሱ መመለስ ነው፤ ከዚህ በኋላ የሚጠፋ እና የሚባክን ጊዜ የለንም፤ የማዕዘኑ ድንጋይ ራስ በሆነው በክርስቶስ፣በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ እንታነጽ (ኤፌ. 2፡20)፡፡

ከጨለማው መንገዳችን መልሶ በልጁ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከራሱ ጋር ያስታረቀን አምላክ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ድረስ የተመሰገነ ይሁን፡፡ አሜን!

ሠላም ወሰናይ!

አባ ዳዊት ወርቁ

ዘማኅበረ ካፑቺን


ቅዱስ አባታችን በኡጋንዳ፦ ድኾችን አትርሱ፣ ክርስቶስ በሚሰቃዩት ውስጥ ነው

$
0
0

እ.ኤ.አ. ህዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም. ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በኬንያ ያካሄዱት ሐዋርያዊ ዑደት አጠናቀው ወደ ኡጋንዳ በመነሳት በኡጋንዳ ሰዓት አቆጣጠር ልክ ከቀትር በኋላ 11 ሰዓት ከ 15 ደቂቃ ኤንተበ በሚገኘው ዓለም አቀፍ ያየር ማረፊያ እንደደረሱ በአገሪቱ ርእሰ ብሔር ዮዎሪ ሞሰቪኒና ክብርት ባለ ቤታቸው በአገሪቱ ብፁዓን ጳጳሳትና በብዙ ሺሕ የሚገመት የአገሪቱ ሕዝብ በመዝሙርና በባህላዊ ሸብሸቦ አቀባበል ከተደረገላቸው በኋላ የቅድስት መንበርና የኡጋንዳ ሕዝባዊ መዝሙሮች ተደምጠዋል።

በመቀጠልም ቅዱስነታቸው ወደ ቤተ መንግሥት በመሄድ ከአገሪቱ ርእሰ ብሔር ጋር የግል ግኑኝነት አካሂደው እንዳበቁም በርእሰ ብሔሩ ተሸኝተው ከመንግሥት አበይት አካላትና በኡጋንዳ ከሚገኙት ከተለያዩ አገሮች ልኡካነ መንግሥታት ጋር መገናኘታቸው የገለጡት የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ ሰርጆ ቸንቶፋንቲ አያይዘው ቅዱስ አባታችን በዚህ የኡጋንዳ ሰማዕታት ቅድስና አዋጅ ዝክረ 50ኛው ዓመት ጋር በተያያዘው ሐዋርያዊ ጉብኝታቸው በቤተ መንግሥት ባሰሙት ንግግር፦ የደም ሰማዕትነት የከፈሉት የካቶሊካዊትና የአንግሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሰማዕታት የአገር ጀግኖች በከፈሉት መሥዋዕትነት አማካኝነትም የእምነት ግብረ ገብ የተካነ ሕይወትና ለጋራ ጥቅም ትጋት የሰጡት ምስክርነት ዛሬ በአገሪቱ የባህል የኤኮኖሚ የፖለቲካ ሕይወት ህላዌው ቀጣይነት አለው፣ ምንም’ኳ የተለያየ ሃይማኖታዊ እምነት ያለን ቢሆንም ቅሉ ሁላችን ይላሉ ቅዱስነታቸው፣ እውነትን ለመሻት ፍትሕ ለመገንባት ዕርቅና መከባበር ለማረጋገጥ እንደ የአንዲት ቤተሰብ አባላት እርስ በእርስ ለመደጋፈና ለመተሳሰብ ተጠርተናል እንዳሉ አስታውቀዋል።

እነዚህ አበይት እሴቶች ለእነዚያ ግልጽነት የተካነው መስተዳድር የተሟላ ሰብአዊ እድገት የሁሉም በማሕበራዊ ሕይወት ሱታፌ የሚል መመዘኛ መሠረት ለሁሉም በዚያ ፈጣሪ በጸጋው ለሰጠው የአገር ሃብት የተስተካከለ ተጠቃሚነት ዋስትና ለማረጋገጥ ኃላፊነት ላላቸው አካላት እግብር ላይ እንዳያውሉ ይጠየቅባቸዋል፣ ዓለም አፍሪቃ የተስፋ ክፍለ ዓለም አድርጎ ነው የሚመለከታት፣ ኡጋንዳ በእውነቱ እግዚአብሔር በሕዝቧ በጽኑ ቤተሰቦቸዋ በወጣቶችዋና በአዛውንቷ ባጠቃላይ የአገሪቱ ዜጎች አማካኝነት ባርካታል፣ በመሆኑም ይኸንን እግዚአብሔር ያደላት ሃብት በሚገባ በመንከባከብና በማቀብ ለማስተዳደር የተጠራችሁ ናችሁ እንዳሉ የገለጡት የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ ቸንቶፋንቲ በማያያዝ፦ ለወጣቱ ትውልድ ተገቢ ሕንጸት ተገቢ የደሞዝ ክፍያ ያለው ሥራ የማግኘት መብት ማስከበር በተለይ ደግሞ በማሕበራዊ ሕይወት ንቁና የተሟላ ሱታፌ እንዲኖረው ማድረግ ያስፈልጋል።

አዛውንት የአገር ዜጎች ቡራኬ ናቸው፣ የሕዝብ ተዘክሮ ያላቸው ጥበብና ገጠመኝ ብሶል ነውና ያለው ክቡር እንዲጠበቅ በማሳሰብ ኡጋንዳ ስደተኞችና ተፈናቃዮች በማስተናገዱ ተግባር የምትሰጠው አገልግሎት አመስግነው፣ የምንኖርበተ ዓለም በዚህ ተጠቅሞ መጣል በሚል መንፈሳውያን እሴቶችን በሚያዳክም የሰውን ልጅ ልብ የሚያደነድን ድኾችን የሚዘነጋ የወጣት ትውልድ ተስፋ የሚነጥቅ ባህል እጅግ እየተበከለ ባለው ዓለም ትብብር መደጋገፍ እንዲረጋገጥ አደራ እንዳሉ የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ ቸንቶፋንቲ አመለከቱ።

ቅዱስ አባታችን ለኡጋንዳ ትምህርተ ክርስቶስ አስተማሪዎች

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በዚህ የኡጋንዳው ሐዋርያዊ ዑደታቸው መርሃ ግብር መሠረት በካምፓላ ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ሰፕሪኣን ኪሲቶ ልዋንጋ የእንኳን ደሃን መጡ መልእክት ከተደመጠ በኋላ በሙንዮንዮ የአንድ አዲስ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ የመሠረት ድጋይ ባርከው ካኖሩ በኋል ከሁሉም የተለያዩ አቢያተ ክርስቲያን መንፍሳውያን መሪዎች ጋር በመሆን እዛው ለሰላም ትእምርት በጋራ ዛፍ ተክለው ውሃም በማርከፍከፍ የተለያዩ ሃይማኖቶች መካከል የጋራው ውይይት ያለው አስፈላጊነት መስክረው፣ የሙንዮንዮ ሰበካ የትምህርተ ክርስቶስ አስተማሪዎችና የሕንጸት አስተማሪዎችን ተቀብለው፦ ቀዳሚውና አቢይ መምህር ኢየሱስ ክርቶስ  መሆኑ በማሳሰብ፣ የትምህርተ ክርስቶስ አስተማሪዎች ተልእኮ ያለው አስፈላጊነት ገልጠው፣ ከብፁዓን ጳጳሳት ከካህናት ከዲያቆናት እርሱም ወንጌል እንዲያበስሩ የማዕርግ ምሥጢር ከተቀበሉት ጋር በመተባበር የእግዚአብሔር መንጋ ለመንከባከብ የጠሩ መሆናቸው እንዳብራሩ  የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ ማሲሚሊያኖ መኒከቱ ገልጠው፣ አዲስ ዜና ወደ ሁሉ የአገራችሁ መንደሮችና መኖሪያ ቤቶች የማበሰሩ ጥሪ የተቀበላችሁ ናችሁ፣ ይኽ ደግሞ በጽናትና በውፉይነት ተግባር ቤተሰቦችና ወላጆች ልጆቻቸውን በእምነት እንዲያሳድጉ ቃልና ሕይወት በተካነው ምስክርነት ወንጌል በማበሰር በተለያየ ዘርፍ ለሕዝበ እግዚአብሔር ቅርብ በመሆን በአገራችሁ መሬት የእምነት ዘር የምትዘሩና የምትኮተኩቱ ናችሁ፣ ለሕፃናትና ለወጣቶች ጸሎት የምታስተምሩ ናችሁ።

ብፁዓን ጳጳሳትና ካህናት ለትምህርተ ክርስቶስ አስተማሪዎች በቤተ ክርስቲያን የአንቀጸ ትምህርት በሐዋርያዊ ግብረ ኖልዎና በመንፈሳዊነት ጎዳና ሕንጸት በማቅረብ ረገድ በመደገፍና በማነጽ እንዳይለዩዋቸው ያሳሰቡት ቅዱስ አባታችን፣ በቅዱስ ቁርባን ሱታፌ ያለው ሐሴት አካፍሉ ብለው ዮሓንስ ወንጌል ምዕ. 1 ቁ. 5. ብርሃን በጨለማ ያበራል ጨለማም ብርሃንን ከቶ አያሸንፈውም የሚለውን ቃል ጠቅሰው ሙንዮንዮ በዚያ ክልል የነበረው ንጉሥ የክርስቶስ ተከታዮችን ለሞት የዳረገበት የኡጋንዳ ሰማዕታት ያፈሰሱት ደም ቦግ ብሎ የሚያበራበት ስፍራ መሆኑ ገልጠው፣ የእነርሱ የእምነት ጽናት በክርስቶስ በተገባው የተስፋ ቃል ላይ ያላቸው እማኔ የሚያረጋግጥ ነው ብለው በስዋሂሊኛ ቋንቋ ኦሚካማ አባወ ኦሙኪሳ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ብለው ቡራኬ ሰጥተው የለገሱት ምዕዳን እንዳጠቃለሉ መኒከቲ አስታወቁ።

ቅዱስ አባታችን ለኡጋንዳ ወጣቶች

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንችስኮ ካምፓላ በሚገኘው ኮሎሎ የአየር ማረፊያ ነበር ባለው አደባባይ ከኡጋንዳ ወጣቶች ጋር ተገናኝተው መሪ ቃል መለገሳቸው የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ አለሳንድሮ ጂሶቲ ገለጡ።

ቅዱስ አባታችን ከአዲት ገና ከመወለድዋ የኤይድስ በሽታ ታማሚ የሆነች ወጣትና አንድ በአገሪቱ በሚገኘው የጌታ ታጣቂ ኃይል በማለት ገዛ እራሱ በሰየመው የአማጽያን ኃይል ተጠልፎ ሕጻን ወታደር በመሆን ያገለገለው ከዚያ ባርነት ነጻ የወጣው ወጣት ከሰጡት የምስክርነት ቃል በኋላ  በለገሱት ምዕዳን፦ በአይድስ በሽታ የተጠቁት ወጣቶች ፍቅር ሊለገስላቸውና ሊደገፉም የተገባ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኃላፊነት ነው።

ኢየሱስ ግድግዳዎችን ወደ አድማስ ይለውጣል

የሁለቱ ወጣቶች ገጠመኝ ጠቅሰው፣ ያንን አሉታዊ ገጠመኝ ኢየሱስ ወደ አዲስ አድማስ ለውጦታል፣ በኢየሱስ ኃይል ሕይወታችን እንደሚለወጥ የሁለቱ ወጣቶች ሕይወት ምስክርነት ተአምራዊ አብነት ነው።

እናንተ የኡጋንዳ ወጣቶች የጥላቻው መንፈስ ወደ ፍቅር ለወጡት

በኢየሱስ ማመን ስጋት ሊሆን ይችላል፣ ሆኖም የሚያድነውም በእርሱ ላይ ያለን እምነት ነው። ሕይወታችን ልክ እንደ አንድ ዘር ነው፣ ለመኖር መሞት ያስፈልጋል፣ አንዳንዴም ሥጋዊ ሞት ሊያጋጥም ይችላል፣ ሆኖም ሞትን የሰማዕትነት ሞት ማድረግ ያለው የላቀው እሴት የኡጋንዳ ሰማዕታት ይመስክሩታል፣ አሉታዊ ገጠመኝ ወደ አወንታዊ ገጠመኝ ለመቀየር ስችል ባለ ድል እሆናለሁኝ፣ ይህ ደግሞ በኢየሱስ ጸጋ የሚቻል ነው ብለዋል።

ጦርነትን ወደ ሰላም። የሰማእታት አገር ልጆች መሆናችሁ ማስተዋል ይኖርባችኋል፣ ስለዚህ ይኽ ያላችሁ የአፈሪቃ ክቡር ሕይወት ነው። ኢየሱስ ያንን ለያይ ግንብ ወደ አድማስ ለውጦታል።

ችግሮችን መወጣት አሉታዊው ወደ አወንታዊ እንዲለወጥ መጸለይ

ከመጸለይ አትቦዝኑ፣ የልባችሁን በር ክፈቱ፣ ኢየሱስ ይገባ ዘንድ ፍቀዱለት፣ እርሱ በምናደርገው የሕወት ትግል ሁሉ ይደግፈናል ኃይልም ይሆንልናል፣ እርሱ በሕይወታችን ውስጥ ሲገባ ሁሉን ለመቋቋም ይቻለናል፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነን፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁላችን እናት አለችን እርሷም ቅድስት ድንግል ማሪያም ነች፣ እርሷን ተማጠኑ።

ስለዚህ ችግሮችን መወጣት፣ አሉታዊው ወደ አወንታዊ መለወጥና መጸለይ የተሰኙትን ሦስት ነጥቦች እትርሱ። ሊያድነኝ ሕይወት ሊሰጥኝ ወደ መጣው ኢየሱስ መጸለይ፣ እርሱ ብቻ ነው ጌታ፣ በቤተ ክርስቲያንም ወላጅ አልባ አይደለንምና እናታችን ወደ ሆነችን ቅድስት ማርያም እንጸልይ በማለት የለገሱት ምዕዳን እንዳጠቃለሉ ጂስቲ ገለጡ።

ቅዱስ አባታችን፦ ድኾችን አትርሱ፣ በሚሰቃዩት ውስጥ ክርስቶስ ህያው ነው

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ከኡጋንዳ ወጣቶች ጋር ያካሄዱት ግኑኝነት አጠናቀው በናልኮሎንጎ ወደ ሚገኘው እ.ኤ.አ. በ 1978 ዓ.ም. በካርዲናል ንሱቡጋ ወደ ተመሠረተው በደጉ ሳምራዊው እረኝ ደናግል ማሕበር ሥር ወደ ሚተዳደረው የግብረ ሠናይ ማእከል በመሄድ በለገሱት ምዕዳን፦ የጌታ ህላዌ የሚደመጥበት የሚነካበት ቤት ነው። ኢየሱስ በታመሙት በድኾች በተናቁት በታሰሩት ተስፋ በቆረጡት ውስጥ መሆኑ ካለ ምንም ጥርጥር ገልጦልናል፣ አደራ ድኾችን አንርሳ። አፍሪቃ ድኾችን አትርሳ።

ወንጌል ወደ የከተሞቻችንና ወደ የሕልውና ጥጋ ጥግ ክልል እንድንል ግድ ይለናል፣ አማራጭ አይደለም፣ ድኾችን ወጣቶችን አረጋውያንን መዘጋት የሚያስከትለው ፍርድ ጌታ ግልጥ አድርጎ ነግሮናል፣ በአለማችን ግለኝነት ለእኔ ባይነት ስግብግነት እየተስፋፋ ነው፣ ብዙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የዚህ አሉታዊ ባህል ሰለባዎች ናቸው፣ ክርስትያን እንደ መሆናችን መጠን ይኸንን ጉዳይ ዝም ብለን መመልከት ሳይሆን በዚህ አሉታዊ ባህል በሚታይበት ዓለም የእግዚአብሔር ታጋሹና የመሃሪው ፍቅር ምልከት ሆኖ መገኘት ይጠበቅብናል፣ ሊገለገል ሳይሆን ሊያገለግል ለመጣው ጌታ ምስክር እንሁን፣ ሰዎች ከነገሮች በላይ መሆናቸው እንመስክር፣ ለእነዚህ ታናናሽ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የምናደርገው መልካም ነገር ሁሉ ለጌታ እንዳደረግነውም የተረጋገጠ ነው ቃሉም የኢየሱስ ቃል ነው።

ወዳጆቼ ተራ በሆነው ተግባር አምላኪያን መሆናችን በሚገልጠው ኢየሱስን በሚያከብር ምልክትና ተግባር ወደ ዓለም ፍቅር እንዲገባ እናድርግ ይኽ የፍቅር ኃይል ዓለም የሚለውጥ ኃይል ነው ብለው የለገሱት ምዕዳን እንዳጠቃለሉ የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ ጂሶቲ አስታወቁ።

በሰማዕታት ደም ለጸናው በተለያዩ አቢያተ ክርስቲያን የሚኖር የጋራ ግኑኝነት ክብር

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በዚህ ዝክረ 50ዓመት የኡጋንዳ ሰማዕታት የቅድስና አዋጅ በሚከበርበት በአሁኑ ወቅት በኡጋንዳ ባካሄዱት ሐዋርያዊ ጉብኝት በኡጋንዳ የሰማዕታት ቅዱስ ሥፍራ እ.ኤ.አ. ህዳር 28 ቀን 2015 ዓ.ም. በአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 9 ሰዓት ተኩል በብዙ ሺሕ የሚገመቱ ምእመናን የአገሪቱ ርእሰ ብሔር ዓበይት የመንግሥት አካላት በተገኙበት መሥዋዕተ ቅዳሴ ማሳረጋቸው የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ ፓውሎ ኦንዳርዛ ገልጠዋል።

 

የካቶሊካዊትና አንግሊካውያን ሰማዕታት ቅዱስ ሥፍራ

ቅዱስ አባታችን በናሙጎንጎ የሚገኘው የአንግሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት ቅዱስ ስፍራ ጎብኝተው እዛው ከአንግሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት ጋር ተገናኝተው የህሊና ጸሎት አሳርገው እንዳበቁ፣ በዚያ ቅዱስ ካርሎ ልዋንጋና 21 ወጣት ክርስቲያን ጓደኞቹ እውነተኛውና ብቸኛው ንጉሥሳቸው ክርስቶስ መሆኑ በመምስከራቸው እ.ኤ.አ. ሰነ 3 ቀን 1886 ዓ.ም. በክልሉ በነበረው ንጉሥ ለሞት በተዳረጉበት የደም ሰማዕትነት በከፈሉበት ቅዱስ ሥፍራ ተገኝተው መስዋዕተ ቅዳሴ አሳርገው፣ የሰማእታቱ ምስክርነት ክርስቶስን ወደ ሁሉም የዓለም ማእዝን ለማድረስ አብነት ነው የሚል ቅዉም ሃሳብ ማእከል ያደረገ ስብከት መለገሳቸው ኦንዳርዛ ገልጠዋል።

ቅዱስ አባታችን ባስደመጡት ስብከት የእነዚያ ወጣት ሰማዕታት ምስክርነት የምናከብረው በዝክረ በዓልና በቤተ መዘክር ለማስቀመጥ እንደ ሚወረስ የእምነት ሃብት ስናቅብ ሳይሆን እነርሱ ለክርስቶስ የከፈሉት መሥዋዕትነት በዚህ በምንኖርበት ዘመን ወደ ቤታችን ለጎረቤቶቻችን በምንሰራበት ሥፍራ በምንኖርበት ማኅበረሰብ እስከ አጽናፍ ዓለም ምስክርነታቸውን ስንመስከር ብቻ ነው።

የኡጋንዳ ሰማዕታት ለክርስትና ሕይወት አደገኛ በሆነበት ዘመን ክርስቶስ ያወጁ

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ቅዱስ ካርሎ ልዋንጋና ጓደኞችን ጠቅሰው የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ለማፈን የማይቻል መሆኑ በማብራራት፣ በእምነት ከታነጹ በኋላ ያንን የተቀበሉት እምነት በዚያ አደገኛ በሆነበት ዘመን መስክረውታል። ምስክርነታቸውም ዛሬም ክርስቶስን የሚያውጅ የመስቀል ኃይል የሚያበስር ነው ብለው፣ የሰማዕታቱ ሕይወት ብቻ ሳይሆን ለእነርሱ በአደራ የተሰጡት የወጣቶች ሕይወት ጭምር ነበር ላደጋ የተጋለጠው፣ ለሌሎች ክርስቶስ ለመመስከር ሕይወታቸው ለመሰዋት አልፈሩም፣ እምነታቸው ምስክርነት ሆነ፣ ዛሬ ሰማዕታት ብለን እናከብራቸዋለን፣ አብነታቸው አሁንም ለብዙ ሰዎችና ለዓለም አስተንፍሶ ነው።

ክርስቶስ ልኡካነ ወንጌል እንድንሆን ይጠራናል፣ ለጓደኞቻችን ለጠላቶቻችን ሁሉ፣ ለዚህ ተልእኮ ክፍት መሆን ከቤተሰብ ከፍቅርና የምህረት ትምህርት ቤት የሚጀምር አዛውንቶችን ለመንከባከብ ድኻው መበለት ወላጅ አልባ ሁሉ ለመንከባከብ የሚያንጽ ነው።

ለሥልጣንና ለዓለማዊ ድሎት ሳይሆን ለጌታ ታማኝ በመሆን ዘላቂነት ያለው ሐሴት እንለግስ

የሰማዕታት ምስክርነት ለሥልጣን ወይን ለዓለም ድሎት ሳይሆን ለእግዚአብሔር ታማኝነትና ቅነነት፣ የሕይወት ምሉእነት ስለ ሌሎች አሳቢና ገር ለመሆን የሚያበቃ ዘላቂ ሐሴትና ሰላም የሚሰጥ ነው።

መጻኢን ብቻ በማተኰር ስለ ወቅታዊው ዓለም ችላ በል የሚል ምስክርነት ሳይሆን ለዚህ ዓለም ህያው ግብ የሚያቀርብ የተናቁትንና ለድኾች ቅርብ ለመሆን የሚያበቃ ስለ የጋራ ጥቅም ከሌሎች ጋር ለመተባበር የሚደግፍ በጋራ ቅንና ፍትህ የተካነው ማንም የማያገል የሰው ልጅ ክብር ለማነቃቃት ሕይወት የእግዚአብሔር ጸጋ ለመከላከል የሁላችን ቤት የሆነው ተፈጥሮና የተፈጥሮ አስደናቂነ ለመንከባከብ የሚያንጽ ነው በማለት ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ያስደመጡት ስብከት ማጠቃለላቸው ኦንዳርዛ አስታወቁ።   

ቅዱስ አባታችን በኡጋንዳ ለውፉይ ሕይወት አባላትና ውሉደ ክህነት

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በኡጋንዳ ባካሄዱት ሐዋርያዊ ዑደት እ.ኤ.አ. ህዳር 28 ቀን 2015 ዓ.ም. የውፉይ ሕይወት የውሉደ ክህነት አባላትና ገዳማውያን እንዲሁም የዘረአ ክህነት ተማሪዎችን ካምፓላ በሚገኘው ካቴድራል ተቀብለው ለውፉይ ሕይወት ኣባላት በታማኝነት መጽናት ማለት አለ ምንም ድብብቆሽና ካለ ምንም አስመሳይ መንትያ ሕይወት አለ መኖር ለገዛ እራስ ኃጢአትም ምህረት መለመን ማለት ነው በሚል ቅዉም ሃሳብ ላይ ያነጣጠረ ሥልጣናዊ ምዕዳን መለገሳቸው የቫቲካን ረዲዮ ልእክት ጋዜጠኛ ጃዳ አኵይላኒ ገልጠዋል።

ለሰማእታት ተዘክሮ ታማኝ መሆን

ተዘክሮና ምስክርነት በታማኝነትና በጸሎት። ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. በለገሱት ምዕዳን እነዚህን ሦስት የጥሪ ኃላፊነት ለዘርአ ክህነት ተማሪዎች ለውሉደ ክህነት ለውፉይ ሕይወት አባላት በማብራራት ኡጋንዳ የአፍሪቃ እንቁ በማለት ገልጠው በደም ሰማዕነት የከፍሉት የቅዱሳን እምነት ላይ በማተኰር የኡጋንዳ ቤተ ክርስቲያን የሰምዕታቱ ተዘክሮ የእነዚህ ስለ ኢየሱስ ፍቅር ሕይወታቸውን የሰዉ ታሪክ የሩቅ ተዘክሮ አድርጋ ልታስብ አይገባትም፣ የዝክረ ሰማዕታት ጸጋ እንለምን። የኡጋንዳ ቤተ ክርስቲያን ለዚህ ተዘክሮ ታማኝ ለመሆን በዝክረ ሰማዕታት ብቃትና ትርፍ መኖር ሳይሆን ምስክር ሆኖ መገኘት አለባት እንዳሉ አኵይላኒ አመለከቱ።

የካህናት እጥረት ወዳለባቸው ሰበካዎች ካህናት መላክ

የቅስት ማሪያም ካቴድራል እ.ኤ.አ. በ 1969 ዓ.ም. በጳውሎስ ስድስተኛና እ.ኤ.አ. በ 1993 ዓ.ም. በቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ መጎብኘቱ ያስታወሱት ልእክት ጋዜጠኛ አኵይላኒ በዚያ ካቴድራል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ሊቀ ጳጳሳት የብፁዕ አቡነ ጆሰፍ ኪዋንካ አጽም ያረፈበት መህኑም ጠቅሰው፣ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮን የተዘክሮ መስካሪያን እንጂ አክባሪያን ብቻ እንሁን ብለው፣ የቅዱሳኑ ሱታፌ በመከትል ምስክርነቱ ለጥሪ ጸጋ ታማኝ በሐዋርያዊ ቀናተኛንነት እንዲገለጥ አደራ፣ ታማኝነት ማለት የካህናት እጥረት ወዳለበት ሰበካ ለማገልገል እሺ በሚል መንፈስ ለብፁዕ አቡን መታዘዝ ማለት ነው በርግጥ ቀላል አይደለም፣ ሆኖም ወንጌላዊ ጥሪ ነው እንዳሉ ገልጠዋል።

ኡጋንዳ የአፍሪቃ እንቁ

የካምፓላ ሰበካ በካህናት ጥሪ እጅግ ሃብታም ነው፣ ስለዚህ የካህናት እጥረት ወዳለበት ሰበካ በመላክ ማገልገል ለክህነት ጥሪ ታማኝ መሆንን እንዲመስክሩ አደራ። ለድኾች ለታመሙት ለተናቁት ታማኝ መሆን፣ ምክንያቱም በእነርሱ ክርስቶስ ህያው ነውና፣ የክህነት ጸጋ በአዲስ የተልእኮ መንፈስ በአዲስ ምስክርነት አዲሱን ተግዳሮት መግጠም ያስፈልጋል፣ ካልሆነ ያንን ጸጋ ማጥፋት ይሆናል። በቤተ መዘክር የሚኖር ይሆናል እንዳሉ አኵይላኒ አስታወቁ።

መንትያ አስመሳይ ሕይወት አለ መኖር፣ ካለ መታከት ምህረት መለመን፣

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ወደ ካቴድራሉ ገብተው ለክብራቸው ለካምፓላ ሰበካ ሊቀ ጳጳሳት የካህናትና የውፉይ ሕይወት ሕንጸት ጉዳይ አለቃ ብፁዕ አቡነ ጆን ባፕቲስት ካግዋ ያስደመጡት የእንኳን ደህና መጡ መልእክትና እንዲሁም የአንዲት ድንግልና የአንድ የውፉይ ሕይወት አባል ምስክርነት መደመጡና ያስታወሱት ልእክት ጋዜጠኛ አኵይላኒ የካምፓላ ሰበካ 1,500 ካህናት እንዳሉትና 7 ሺሕ የሚገመቱ የተለያዩ የኡጋንዳ የውፉይ ሕይወት አባላት በህክምና በሕንጸት በሐዋርያዊ ግብረ ኖልዎ በማህበራዊ ጉዳይ ተሰማርተው በማገልገል ላይ እንደሚገኙ ብፁዕ አቡነ ካግዋ የገለጡት ሃሳብ ቅዱስ አባታችን ጠቅሰው፣ ይኸንን ሃብት ለቅድስና አውሉት፣ በዚህ የምጽአትና የምህረት ቅዱስ ዓመት ዋዜማ በዚህ የውፉይ ሕይወት ዓመት ጸላያን ሁኑ፣ ብዙ ሥራ ሳላለብኝ በሚል ምክንያት ጥቂት ጸሎት ወይንም አለ መጸለይ የሚኖር ካህን ሊኖር  አይገባም፣ የሚኖር ካለ የኡጋንዳ ሰማእታት ተዘክሮና ታማኝነትን የዘነጋ ማለት ነው እንዳሉ አኵይላኒ አስታወቁ።

ጸሎት ማለት ትህትና ማለት ነው፣ አግባብ ባለው መንገድ በሚሥጢረ ንስኃ መሳትፍ ትህትና ነው፣ በሁለት እግር ማነከስ አይቻልም፣ አንድ ካህን አንዲት ድንግል መንትያ ሕይወት መኖር አይችልም አትችልም፣ ኃጢአተኛ ከሆንክ ምህረትን ለምን ኃጢአተኛ ከሆንሽ ምህረት ለምኚ። ጥሪ የወለም ዘለም ሕይወት አይደለም፣ እግዚአብሔር የማይፈልገው ሕይወት ደብቃችሁ አትኑሩ፣ ያለ መታመን ታማኝነትን ማጉደልም ደብቃችሁ አትኑሩ፣ ተዘክሮ በቁም ሳጥን ውስጥ አትዝጉ ያሉት ቅዱስ አባታችን የለገሱት ምዕዳን ሰላም የተጠሙት አገሮችና ሕዝቦች ቡሩንዲን ጠውሰው እግዚአብሔር በመሪዎችና በመንግስታት በሕዝቦች ልብ ውስጥ የሰላም ፍላጎት የመተባበርና የውይይት የእርቅ ፍላጎት ያሳድር በማለት ማጠቃለላቸው አኵይላኒ ገለጡ።

ፍራንቸስኮ ሰይሙኝ

$
0
0

በታኦድወፊልም የተቀረጸው በመዱሳ የፊል አሰራጭ ድርጅት ለትሪኢት የሚቀርበው ፍራንቸስኮ ሰይሙኝ በሚል ርእስ ሥር የተደረሰውና የተቀረጸው ፊልም እ.ኤ.አ. ታህሳስ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. በአገረ ቫቲካን በሚገኘው ጳውሎስ ስድስተኛ የጉባኤ አዳራሽ ለቀዳሜ ትርኢት እንደቀረበ ጳጳሳዊ የምጽዋት ጉዳይ የሚከታተል ቢሮ ካሰራጭው መግለጫ ለመርዳት ሲቻል፣ ፊልሙ እ.ኤ.አ. ከታህሳ 3 ቀን 2015 ዓ.ም. በተለያዩ ሲነማ ቤቶች ለትርኢት እንደሚቀርብ ያመለክታል።

በፊልሙ ቅድመ ትርኢት ፊተኞች ድኾችና መጠለያ የሌላቸው የጎዳና ተዳዳሪዎች

ጳጳሳዊ የምጽዋት ጉዳይ የሚከታተለው ሐዋርያዊ ጽሕፈት ቤት ባስራጨው መግለጫ እንዳመለከተውም ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በፊልሙ ቅዳሜ ትርኢት ቀዳሚ ታዳሚዎች ድኾችና መጠለያ አልባ የሆኑት የጎዳና ተዳዳሪዎች ስደተኞች ተፈናቃዮችና ስለ እነዚህ የኅብረተሰብ ክፍል የሚጣብቁትና እነርሱን በማገልገል ተልእኮ የሚጠመዱት የበጎ ፈቃድ ማኅበራት የመንፈሳዊ ማኅበር አባላት ዕለት በዕለት በግብረ ሰናይ ተልእኮ የሚያገለግሉት እንዲሆኑ በማለት የሰውጡት ውሳኔ መሠረት 7 ሺሕ ቲኬት ለተሳተፉት ድኾችና መጠለያ አልባ አነርሱን በግብረ ሠናይ ተልእኮ ለሚያገለግሉት ሁሉ መልካም ፈቃድ ባላቸው ሰዎች ግዥ መታደሉና አነዚህ በጎ አድራጊዎች መልካም ፈቃድ መሠረትም የእራት መዓድ መቅረቡ ሲታወቅ፣ ጳጳሳዊ የስዊዘርላድ ጸጥታ ኃይል የሙዚቃ ቡድን ለተጋባእያኑ ጥዑም የመሣሪያ ሙዚቃ ያስደመጡ ሲሆን፣ በእራት ማዕድ ግብዣም የፊልሙ ደራሲና ቀራጭ ዳኔለ ሉከቲ እንዲሁም በተደረሰው ፊልም ተወናያን በመሆን ያገለገሉት ከሁሉም ጋር በመተዋወቅ ሰላምታ እንድቀረቡና በመጨረሻም ለሁሉም በአዳራሹ ለተገኙት የእኛ ቢጤዎች መልካም ፈቃድ ባላቸው ሰዎች የተለገሰ ገጸ በረክትም መታደሉ ጳጳሳዊ የምጽዋት ጉዳይ ተንከባካቢ ጽ/ቤት ያሰራጨው መግለጫ ይጠቁማል።


የሰላም ነጋዲ

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ እ.ኤ.አ. ህዳር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የኡጋንዳው ሐዋርያዊ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ከኢንተበ ዓለም አቀፍ የአየር ማረፊያ በአገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ልክ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ተነስተው በማእከላዊት ረፓብሊክ አፍሪቃ ርእሰ ከተማ ባንጒይ በሚገኘው ዓለም አቀፍ ያየር ማረፊያ እ.ኤ.አ. ጥር 2014 ዓ.ም. በተመረጡት የአገሪቱ የሽግግር መንግሥት ርእሰ ብሔር ካተሪን ሳምባ ፓንዛ ባንጒይ በሚገኙት የቅድስት መንበር ሐዋርያዊ ልኡክና በማእከላዊት ረፓብሊክ አፍሪቃ የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን ጳጳሳት በብዙ ሺሕ በሚገመቱት የአገሪቱ ዜጎች አቀባበል ተደርጎላቸው ለአገሪቱና ለርእሰ ብሐር ክብር ወደ የአገሪቱ ቤተ መንግሥት በማምራት ከርእሰ ብሔር ሳምባ ፓንዛ የግል ግኑኝነት ካካሄዱ በኋላ በቤተ መንግሥት የጉባኤ አዳራሽ የአገሪቱ መንግሥትና የፖለቲካ አበይት አካላት ባንጉይ የሚገኙት የተለያዩ መንግሥታት ልኡካን በተገኙበት ርእሰ ብሔር ካተሪነ ሳምባ ፓንዛ፦

በፍርሃት ላይ የእምነት ድል አድራጊነት

የቅዱስነታቸው በአገሪቱ መገኘት በእውነቱ ቀኑ ታሪካዊና ልዩ ዕለት ነው በማለት ገልጠው፣ በፍርሃት ላይ ድል አድራጊው የኵላዊት ቤተ ክርስቲያን እምነት መተሳሰብና ትብብር የሚመሰክር ነው።

ከቅዱስ አባታችን የጽናት ምስክርነት

አጠያያቂውና አሳሳቢው ወቅታዊው የፖለቲካዊ ጉዳይና ተጨባጭም ይሁን የተጋነነው አስጊ አደጋ ቅዱስነታቸው በመካከለኛይቱ ረፓብሊክ አፍሪቃ ጉብኝት ከማካሄድ አልከለከላቸውም፣ ይኽ ደግሞ ለሁሉም የጽናት ምስክርነትና ትምህርትም ነው ብለው ቅዱስነታቸው በማእከላዊት ረፓብሊክ አፍሪቃ ባለው ቀውስ ለአደጋ የተጋለጡትና ሰለባ ስለ ሆኑት ሁሉ ያሳዩት አሳቢነት የሚገልጥ ነው በማለት አመስግነው፣ ለሁሉም የአገሪቱ ዜጎች ጥልቅና ተጨባጭ አብነት ነው ብለዋል።

ስለ ሁሉም እሰቃቂ ተግባር ሁሉ ምኅረትና ይቅር መባባል

ለሁሉም የአገሪቱ የፖለቲካ አካላትና እንዲሁም በአገሪቱ አመጽ እንዲቀጣጠል በተለያየ መልኩ በተለያየ ደረጃ እጅ ያለባቸውና ጠንሳሾች በጠቅላላ በሃይማኖት ስም አማኞች የፈፍጸሙት ቅትለት የስግደትና የአምልኮ ሥፍራዎችን ያረከሰ ተግባር ሁሉ ከቅዱስ አባታች ይቅርታን በመለመን ምኅረትና ይቅር መባባል እንዲረጋገጥ ለሁሉም አደራ ብለው፣ በፍቅር ላይ የጸና ተጨባጭ መንፈሳዊ መንገድ በጋራ ለመከተል ምኅረትና ይቅር መባባል የማያሻማ ክብር ነው ብለዋል።

የመለያየትና የመከፋፈል ሰይጣናዊ ተግባር ለመገሰጽ የጸሎት ጸጋ

የቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. በመካከለኛይቱ አፍሪቃ ጉብኝት ያሰጠው አቢይ ጸጋ የጸሎት ጸጋ ነው። ሁሉም ለዚህ ጥልቅ ጸጋ አነቃተዋል። ያ የሚለያይና የሚከፋፍል የሰይጣን መንፈስ የሚገስጽ የጸሎት የምህለላ መንፈስ በተግባር ያነቃቃ ጸጋ እንዲሰፍን አድርገዋል፣ ይኽ ደግሞ በእውነቱ ለአገሪቱ ለሰላም ሂደት ወሳኝ ነው ብለዋል።

ዳግም የዴሞክራሲ ሥርዓትና ጸጥታና ደህንነት በመካከለኛይቱ አፍሪቃ

የመካከለኛይቱ ረፓብሊክ አፍሪቃ ሕዝብ ለአገሪቱ መረጋጋትና ሰላም መሠረት የሆነው አገሪቱ አለ ምንም ቂም በቀልና መከፋፈል የጥላቻ መንፈስና የሃይማኖማኖትና የጎሳ አድልዎ ሁሉም ዜጋ በእኩልነት ለአገር ግንባታ የሚጠበቅበት አስተዋጽኦ እንዲያበረክት የሚደግፈው የዴሞክራሲ ሥርዓትና ጸጥታና ደኅንነት ነጻ ሕዝባዊ ምርጫ እንዲረጋገጥ ተስፋ አድርገዋል፣ እውን እንደሚሆን በበኵላቸውም ያላቸው ተስፋ ገልጠው ደግመው ቅዱስ አባታችንን እንኳን ደህና መጡ በማለት ካስደመጡት ንግግር በመቀጠል ቅዱስ አባታችን አንድነት ሰብአዊ ክብርና ሥራ በተሰኙት ሦስት አበይት ቃላቶች ላይ በማተኰርም ባስደመጡት ንግግር፦

አንድነት በብዙኅነት ቀጣይና አቢይ ተግዳሮት ነው፣ ስለዚህ ይኸንን ተግዳሮት ገጥሞ ለማሸነፍ የፈጠራ ብቃት ቸርነትና መስዋዕትነት ሌላውን ማክበር ይጠይቃል፣ ከዚህ ጋር በማያያዝም ሰብአዊ ክብር የሚለውን ቃል ጠቅሰው፣ የገዛ እራሳቸው ሰብአዊ መብትና ክብር ብሎም ያለባቸው ግዴታ ጠንቅቀው የሚያወቁ በዚህ መሠረትም ለእርስ በእርስ መከባበር የሚያተኩሩ ዜጎች የሚለያቸው ግብረ ገባዊ ክብር ቅንነት ታማኝነት ሐቀኝነት ጸጋና ክብር የሚከተሉ ናቸው ብለው በመጨረሻም ሥራ በተሰኘው ቃል ላይ በማተኮር ለሁሉም ዜጎች ትምህርት የጤና ጥበቃ አገልግሎት መጠለያ ምግብ  የማግኘት መብት ማክበር ጋር የተያያዘ መሆኑ አብራርተው ይኽ ደግሞ ለተሟላ ሰብአዊ እድገት አቢይ ድጋፍ ከመሆኑም ባሻገር ለመደጋገፍና ለመተባበር የሚያነቃቃ ነው ብለዋል።

ማእከላዊት አፍሪቃ በተፈጥሮ ሃብት የታደለች አገር ነች፣ ይኸንን ሃብቷም በተገቢ አጠቃቀም ላይ በተመረኰዘ የተሟላ የአገር እድገት ማረጋገጥ ለሚል ዓላማ እንዲውልና የዚህ ሃብት ተጠቃሚም መላ ኅብረተሰብ መሆን አለበት፣ ከዚህ ጋር በማያያዝም ይሴባሕ በሚል ርእስ ሥር የደረሱት ዓዋዲ መልእክት በማስታወስ የተፈጥሮ ሃብት በመጠቀም የሚከወነው እድገት ሁሉም በብሔራዊ አቀፍም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ ምኅዳር መከላከል በሚል እሳቤ የሚመራ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ያስደመጡት ንግግር፦ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ በማእከላዊት ረፓብሊክ አፍሪቃ ሕዝባዊ እርቅ እንዲረጋገጥ ለሰላም መሠረት  መስፈርቶች ከሆኑት ውስጥ አንዱም ጥትቅ መፍታት የሚል ውሳኔ ሥር የተመራ ድጋፍ በማቅረ አገሪቱና ሕዝቧ ወደ ሰላም እንዲያቀና ትብብርና ደጋፍ ያስፈልገዋል፣ ለሰላም ሂደት ፍትህ መሠረት ያደረገ ማኅበራዊ ሰብአዊና ፖሊቲካዊ ሂደት አስፈላጊ ነው በማለት አጠቃለዋል።

ሁላችን ወንድማማቾች ነን

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ እ.ኤ.አ. ሕዳር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ባንጕይ በሚገኘው ቅዱስ ሳቨሪዮ ቁምስና ባለው የስደተኞችና ተፈናቃዮች መጠለያ ሰፈር ጎብኝተው እዛው ከተፈናቃዮችና ከስደተኞች ጋር ተገናኝተው ሁሉም ሰላም በመገንባቱ ሂደት ተገቢ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ስለ ሰላም መሥራትና መጸለይ ያስፈልጋል፣ ሰላም አለ ፍቅር፣ አለ ይቅር መባባል አለ ወዳጅነትና መከባበር አለ ምኅረት የማይቻል ነው። ስለዚህ ሁሉም ሰላም በማረጋገጡ ዓላማ አደራ ይጠመድ፣ ሰላም ከሌለ የሁሉም ተሳትፎ የሚከወን አይሆንም፣ በአገሪቱና በዜጎችዋ መካከል ሰላም እንዲኖር አደራ፣ አለ የጎሳ አለ የባህልና የሃይማኖት የማኅበራዊ ደረጃ ልዩነት ሁሉም በጋራ ስለ ሰላም ይትጋ በሚል ሃሳብ ዙሪያ ንግግር አሰምተው እንደነበር የቫቲካን ረዲዮ ጋዜጠኛ ሚከለ ራቪያርት ካጠናቀሩት ዘገባ ለመረዳት ተችለዋል።

ቅዱስ አባታችን በዚህ በመካከለኛይቱ ረፓብሊክ አፍሪቃ ባካሄዱት ሓዋርያዊ ጉብኝት በአገሪቱ ከሚገኙት የወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ መሪና ምእመናን ጋር እንዲሁም በአገሪቱ ከሚገኙት የምስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና መንፍሳውያን መሪዎች ጋር የተገናኙ ሲሆን፣ ቅዱስ አባታችን በባንጒይ በሚገኘው መስጊድ በአምስት የምስልምና ሃይማኖት መሪዎች አቀባበል ከተደርገላቸው በኋላ ለምስልምና ሃይማኖት ተከታዮች አለ ምንም ፍርሃት ወንድማማቾች ነን የሚለውን ቃል ማእከል በማድረግ ባስደመጡት ንግግር፦

ወንድማማቾች በመሆናችን በጋራ ጥላቻን እንቢ እንላለን

የእግዚአብሔር ሰው ነኝ የሚል ሃይማኖት አለኝ እምነት አለኝ የሚል የሰላም ሰው መሆን አለበት፣ የሰላም ሰው አለ መሆን ከሃይማኖትና ከእምነት ጋር የማይጣጣም ተግባር ነው። ከዚያ የእግዚአብሔር ገጽ ከሚያወላግድ ጸያፍ ተግባር ሁላችን እንቆጠበ አደራ ካለ ምንም የግል ጥቅም መሻት የጋራ ጥቅም እናስቀድም፣ ባንድነት የጥላቻን መንፈስ እንቢ እንበል፣ ቂም በቀል አመጽ በተለይ ደግሞ በእግዚአብሔር ሥም ከሚፈጸም አመጽ ገዛ እራሳችን እንቆጥብ። እግዚአብሔር ሰላም ነው ብለዋል።

ሰላም ገንቢዎች የተመሰግኑ ናቸው

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ለሁሉም ለክርስቲያን ለምስልምናና ለባህላውያን ሃይማኖት ተከታዮች በዚያች አገር በጋራ በሰላም ለመኖር የቻሉ መሆናቸው አስታውሰው፣ በሰላም ጎዳና የሚተጉ ሰላምን የሚገነቡ የተመሰገኑ ናቸው። ለሰላም ገንቢዎች ያላቸው አድናቆትና አክብሮት ገልጠው፣ ልዩነትና ጥላቻ ባላበት ወቅት አለ ምንም ፍርሃት ለማህበራዊ ሰላም የምትተግቡ በመሆናቸሁ ደስ ይበላችሁ በአገራችሁና በአካባቢያችሁ ሰላም የመንገንባት ቅዱስ ተግባር ቀጥሉበት።

ሕዝባዊ ምርጫ የአንድነት ጊዜ ነው

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በአገሪቱ በቅርቡ የሚካሄደው ሕዝባዊ ምርጫ በማሰብም በዚህ ግጭት በሚታይበት ወቅት ዴሞክራሲ የሰፈነበት ሕዝባዊ ምርጫ የተስፋ ምልክት ነው። ስለዚህ አንድነት የሚያበክር ጊዜ ይሁን ብለው አገራችሁ አለ ምንም የጎሳ የሃይማኖትና የፖለቲካ ልዩነት የሁሉም ዜጎችዋና የልጆቿ ቤት ታደርጉ ዘንድ በርቱ ብለው ያስደመጡት ንግግር አጠቃለዋል።

እ.ኤ.አ በየወሩ የመጀመርያ እሁድ በግዕዝ ሥርዓት የሚያርግ መ.ቅዳሴ ታሕሳስ 6 ቀን 2015 ዓም

$
0
0

ማሳሰቢያ ክቡራትና ክቡራን ኣድማጮቻችን፡ እ.ኤ.አ በየወሩ የመጀመርያ እሁድ በጳጳሳዊ ኢትዮጵያዊ ኮለጅ ካህናት ከቫቲካን ረድዮ ጣቢያ በቀጥታ የሚተላለፍ፤ በግዕዝ ሥርዓት የሚያርገው ጸሎተ መሥዋዕተ ቅዳሴ እሁድ ተነገ ወዲያ እ.አ.አ ታሕሳስ 6 ቀን 2015 ዓም ከእኩለ ቀን ተኵል እስከ ሰባት ሰዓት ከ50 ደቂቃ በሮም ሰዓት አቆጣጠር ደግሞ ከ10:30 እስከ 11:50 እንደሚተላለፍ እናሳስባለን።

መሥዋዕተ ቅዳሴው የሚተላለፍበት ሞጎዶች ደግሞ በ15,595 ኪሎ ሄርዝ ወይም በ19 ሜትር ባንድ በ17,590ሎሄርዝ ወይም በ17 ሜትር ባንድ በሮማና ኣከባቢው ለምትገኙ ኣድማጮቻችን ደግሞ በ103.8 ሜጋ ሄርዝ dab በተሰኘው ማለት ዲጂታል አውድዮ ብሮድካስቲንግ አር ቫቲካና ዎርልድ፡ በአይ ኦ ሲ ማለትም በአትላንቲክ ኦውሽን ረጅዮን ሳተላይቶች በአንደኛ በሁለተኛ እና በሶስተኛ መስመሮች፤ በሶስት በዳብልዩ ኤል አይ ማለት በወብ ላይቭ በሁለተኛው መስመር በአንድሮይድ ደግሞ በራድዮ ቫቲካና አፕሊከይሽን አር ቪ አፕስ በሁለተኛ መስመር በቀጥታ ይተላልፋል፣ ክቡራትና ክቡራን አድማጮቻችን በኢንተርነት ለመከታተል www.radiovaticana.va በመክፈት በቋንቋዎች ዝርዝር አማርኛ የሚለውን መገናኛ ስትነኩ በቀጥታ ለመከታተል እሚለው መገናኛ ከነካችሁ ዝግጅቱን ለመከታተል ትችላላችሁ እንዲሁም በአንድሮይድ አፕሊከይሽኑን ለመጠቀም የምትፈልኩ በድረገጹ በስተታች በኩል ካሉ አገልግሎቶች መርጣችሁ በአይፎናችሁ ወይንም በአይፖዳችሁ ለመጠቀም ትችላላችሁ፣

እንዲሁም በናይል ሳት 7 ወስት ኤውተልሳት 7ኤይ ወስት በ11.354 ጊጋሄርትዝ ፖላራይዘይሽን ቨርቲካል ስይምቦል ረይት 27.500 ኤፍ ኢ ሲ 5 እስባር 6 ራድዮ ቫቲካና ወይንም ቫቲካን ረድዮ በሚል ስም ስለሚተላለፍ እንድትከታተሉትና ኣብራችሁ እንድትጸልዩ ኣደራ እንላለን።

የቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ምዕዳን ለካቶሊክ ኣቢያተ ትምህርት

$
0
0

የካቶሊክ ኣቢያተ ትምህርት ወላጆች ማኅበር ዝክረ 40ኛው ዓመት ምሥረታ ምክንያት ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ አገረ ቫቲካን በሚገኘው ጳውሎስ ስድስተኛ የጉባኤ አዳራሽ እ.ኤ.አ. ታህሳስ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ተቀብለው፦ የካቶሊክ ኣቢያተ ትምህርት ለሁሉም ክፍትና ተማሪዎችን አለ ምንም ርእዮተ ዓለም፣ ንግግር በማሣመርም ሳይሆን በእውነተኛው ሰብአዊና ክርስቲያናዊ መንፈስ ማነጽ ይገባቸዋል። ስለዚህ እነዚህ ትምህርት ቤቶች ምንም’ኳ የተለያየ ቀውስ ምክንያት አበይት ችግሮች ቢከሰቱም መለያቸው የሚሸጡ እንዳይሆኑ በማለት ማሳሰባቸው የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ አለሳንድሮ ደ ካሮሊስ አስታወቁ።

ካቶሊካዊነት ብዙ ተደማጭነት እንዲኖረው ለማድረግ እንደ ሰንደቅ ዓላማ የሚውለበለብ ሳይሆን ልዩ የሚያደርገው የሚሰጠው የሕንጸት ብቃትና ጥራት ነው። በመሆኑም የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አቢያተ ትምህርት በርእዮተ ዓለም የሚነዳ ሕንጸት የሚቃወሙ ናቸው ያሉት ቅዱስ አባታችን፦

የተማሪዎች ወላጆች ልጆቻቸው በካቶሊክ አቢያተ ትምህርት እንዲታነጹ የሚወስዱት ውሳኔ ቀዳሚውና የማይካደውን የኅሊና ነጻነታቸውን በመጠቀም ነው። በመሆኑም ማንም የማይነጥል ሕንጸት ማነቃቃት በቤተሰብና በትምህርት ቤት፣ በትምህርት ቤትና በክልል በትምህርት ቤትና በብሔረ ተቋማት መካከል አገናንኝ ድልድይ ሆነው መገኘት ይኖርባቸዋል። በአሁኑ ወቅት የሕንጸት ውል  ላደጋ ከመጋለጡም አልፎ ተጥሰዋል፣ ስለዚህ ዳግም መልሶ ክብሩን ለማጎናጸፍ የሁሉም ተሳትፎ ያስፈልጋል፣ ይኽ ርብርቦሽ መከፋፈል በማስወገድ ጥዑም ውህደት እንዲኖር የሚያደርግ መሆን ይገባዋል፣ ማለትም ለምርጦች ብቻ የሚል ከፋፋይና ነጣይ አመክንዮ ማግለል ግድ ይሆናል እንዳሉ ደ ካሮሊስ አስታወቁ።

ካቶሊካዊ መምህር የሚለው ቅጽል ስም አደራ እንደ ተራ ነገር እንዳይታሰብ፣ ከሌላው ለየት የሚያደርግ ቅጽል ስም ነው። በመሆኑም ጌታ እምለምነው ይኸንን መለያ በሚገባ እንዲከበር ነው። ያለው ልዩነት አጣጥሞ መምራትና ማስተዳደር፣ ይኽ ደግሞ ለካቶሊክ አቢያተ ትምህርት አቢይ ተግዳሮት ነው። ስለዚህ የዓለም ሳይኰን ነገር ግን በዓለም በመኖር እርሾ ሆኖ መገኘት ያስፍልጋል ያሉት ቅዱስ አባታችን በማያያዝ፦

ሰውን ማእከል ማድረግ እንጂ ንግግር ለማሳመር አለ መጠጣር

ስለዚህ የሚለያችሁ እምነታቸሁ ብቻ ሳይሆን ያላችሁ ጥራት ጭምር መሆን አለበት፣ ይኽ ደግሞ ሰውን ማእከል ማድረግ እንጂ ንግግር ማሳመር መሆን የለበትም፣ በተግባር የሚኖር ክብር ማስተላለፍ ማለት ነው እንዳሉ ደ ካሮሊስ አመለከቱ።

ሰብአዊና ክርስቲያናዊ እሴቶች አለ ማዋዋል

ብዙ የካቶሊክ አቢያተ ትምህርት በተለያየ ችግር ምክንያት የሚዘጉ እንዳሉ ያስታወሱት ቅዱስ አባታችን፣ ብዛት ላይ ማተኰር ሳይሆን ጥራት ላይ ማነጣጠርም ያስፈልጋል ብለው ሰብአዊና ክርስቲያናዊ እሴቶች በቃልና በተግባር የሚመሰከርባቸው ከሆነ የሚያጋጥም ማንናው ዓይነት ተግዳሮት ሁሉ ይሸገራል በማለት የሰጡት ምዕዳን እንዳጠቃለሉ ደ ካሮሊስ አስታወቁ።

ኢዮቤልዩ የምህረት ቅዱስ ዓመት

$
0
0

የምህረት ቅዱስ ዓመት መንፈሳዊ ሓሳብ የመጨረሻ የሆኑትን ማገልገል፣ ድኾች የተናቁት የተረሱት የተነጠሉትን በከፋ ድኽነት የሚገኙትንን ኅሙማን፣ ወላጅ አልባ የሆኑትን መበለቶችን አረጋውያንን ማገልገል የሚል መሆኑ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ለቅድስት መንበር የዜናና ኅትመት ክፍል ምክትል አስተዳዳሪ አንጀሎ ሸልዞ ኢዮቤልዮ፣ ምሕረት ቅዱስ ዓመት ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በሚል ርእስ ሥር የደረሱት መጽሐፍ በይፋ ለንባብ በበቃበት እ.ኤ.አ. ታህሳስ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ባስተላለፉት መልእክት እንዳሰመሩበት የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ ፓውሎ ኦንዳርዛ አስታወቁ።

ኢዮቤልዮ፣ ምሕረት ቅዱስ ዓመት ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በሚል ርእስ ሥር የቅድስት መንበር የዜናና ኅትመት ክፍል ምክትል አስተዳዳሪ አንጀሎ ሸልዞ የደረሱት መጽሓፍ በይፋ ለንባብ ለማብቃት በተካሄደው ዓውደ ጉባኤ የተገኙት የቅድስት መንበር ዋና ጸሓፊ ብፁዕ ካርዲናል ፒየትሮ ፓሮሊን፦ በዚህ በአሁኑ ወቅት ቤተ ክርስቲያን ወደ ከተሞቻችንና  በህልውና ጥጋ ጥግ ወደ ሚገኙት እንድትል የሚያሳስብ ጥሪ የሚያመለክት መሆኑ ባስደመጡት ንግግር ገልጠው፣ የማንም ሃይማኖት ተከታይ የማያገል ቅዱስ ዓመት ነው እንዳሉ ኦንዳርዛ አስታወቁ።

ስለዚህ ሁሉም የተለያዩ ሃይማኖቶች በጋራ የሰላም ጎዳና የሚገነቡበት በመተባበር በዓለም የሚታየው ሽበራ ቂም በቀል ሌላውን የማግለል ወጋኝነትን የመሳሰሉት በሃይማኖት ስም ሳይቀር የሚከሰቱት ጸረ ሰብአዊ ተግባር ሁሉ እንዲቀረፍ በጋራ መጠመድ ያለው አስፈላጊነት የሚያሳስብ ቅዱስ ዓመት መሆኑ ሲያብራሩ፣ በመቀጠልም በዓውደ ጉባኤው የተገኙት ለሮማ ክፍለ ሃገር የመንግሥት ምሰሊየነ ፍራንኮ ጋብሪኤሊ ቅዱስ ዓመት ለሮማ ከተማ ችግር የሚፈጥር ሳይሆን እድል ነው። የነጋድያና የቅዱሳት ሥፍራዎች ሁሉ ጸጥታና ደህንነት በሚገባ ዋስትና ለማሰጠት ብቃት ያለው ቅድመ ዝግጅት መከናወኑ ሲያብራሩ። የመጽሓፉ ደራሲ የቅድስት መንበር የዜናና ኅትመት ክፍል ምክትል አስተዳዳሪ አንጀሎ ሸልዞ በበኩላቸውም፦ የሁሉም ሰው ልጅ የመብትና የክብር እኩልነት የሚያበክር ለተናቁትና በከፋ ሰብአዊና ቁሳዊ ድኽነት ሥር ለሚገኙት ሁሉ ማገልገል፣ ከገዛ እራስ ወጥቶ ከሌላ ጋር ለመገናኘት ያለው አስፈላጊነት የሚያሳስብ ሁሉም ለዚህ ቅዱስ ተግባር የሚያነቃቃ ቅዱስ ዓመት ነው ብለው የደረሱት መጽሓፍ የምሕረት ዓመት በሚገባ ለመከታተል የሚያግዝ የመመሪያ መጽሓፍ ነው እንዳሉ የቫቲካን ረዲዮ ልኡክ ጋዜጠኛ ኦንዳርዛ አስታወቁ።

የምኅረት ዓመት ቅዱስ በር የመክፈት ሊጡርጊያዊ ሥነ ሥርዓት

$
0
0

እ.ኤ.አ. ታህሳስ 8 ቀን 2015 ዓ.ም. የምህረት ዓመት ምክንያት በሚፈጸመው የቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ቅዱስ በር በመክፈቱ የሊጡርጊያዊ ሥነ ሥርዓት ቅዱስነታችው ልሂቅ ር.ሊ.ጳ. በነዲክቶስ 16ኛ እንደሚሳተፉ የቅድስት መንበር የዜናና ኅትመት ክፍል መግለጫ አስታወቀ።

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ስለ ምህረት ዓመት በማስደገፍ አስተምህሮ ምዕዳንና ስብከት ሲሰጡ በምህረትና በእውነት መካከል ስላለው ግኑኝነት በተመለከተ ቅዱስነታቸው ልሂቅ ር.ሊ.ጳ. በነዲክቶስ 16ኛ ዋቢ በማድረግ ሲያብራሩ ተደምጠዋል። በተለይ ደግሞ ህዳር ወር 2015 ዓ.ም. ቤተሰብ ርእስ ዙሪያ የመከረው የመላ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን ጳጳሳት ሲኖዶስ ባስጀመሩበትና በመጀመሪያው የሲኖዶሱ ቀናት ወቀት ቅዱስነታቸው ልኂቅ ር.ሊ.ጳ. በነዲክቶስ 16ኛን በስፋት ጠቅሰው እንደነበር ያስታወሰው የቅድስት መንበር መግለጫ አክሎ፦ ቅዱስነታቸው ልኂቅ ር.ሊ.ጳ. በነዲክቶስ 16ኛ እውነት በሐቅ የተሰኘውን ዓዋዲ መልእክት ጠቅሰው እውነት ሰውን ልጅ ይከላከላል ሰብአዊ ፍጡር ከተለያዩ ርእሰ ዋቢነት ከማድረግና ፍርያማው ፍቅር ወደ ስግብግነት ከሚለውጥ፣ ቃል ኪዳን ወደ ጊዚያዊ አብሮ መርኖ ከሚለወጡ ፈተናዎች ይጠብቃል በማለት። አለ ሓቀ ፍቅር ወደ ራሮትና ኢተኣማኒ ስሜት ይቀየራል፣ ስለዚህ እንዲህ ሲሆን ፍቅር በተለያዩ አስፈላጊነት በሌላቸው ነገሮች የተሞላ ባዶ ጨዋታ ሆኖ ይቀራል፣ ባንድ አልቦ እምነት በሆነ ባህል ውስጥ ፍቅር ለዚህ ዓይነቱ ዕጣ ይጋለጣል ያሉትን ጠቅሰው ማብራራታቸው ይገልጣል።

በሲኖዶሱ ፍጻሜ ባስደመጡት ምዕዳን ቅዱስነታቸው ልኂቅ ር.ሊ.ጳ. በነዲክቶስ 16ኛን ጠቅሰው፦ ምኅረት እርሱም እግዚአብሔር የወንጌል መልእክት ማእከል ነው በማለት ሁሉም ቤተ ክርስቲያን የምትለውና የምታከናውነው ያንን እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ያለው ምህረት የሚገልጥ ነው። ቤተ ክርስቲያን የምትለውና የታሳውቀው እውነት በዚያ ከእግዚአብሔር መሃሪው ፍቅር ተገፋፍታ ነው ምክንያቱም ሰዎች ሕይወት እዲሆናቸውና እንዲበዛላቸው ነውና” (ዮሐ. 10,10)።

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. እ.ኤ.አ. መጋቢት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. የምኅረት ቅዱስ ዓመት ሲያውጁ ውድ ወንድሞቼና እህቶቼ ብዙውን ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ምሕረት መስካሪ የመሆን ጥሪዋ እንዴት በማረግ ነው በሚገባ የሚበከረው በማለት ያስቡ እንደነበር ገልጠው፣ ይኽ ደግሞ በአንድ መንፈሳዊ መለወጥ የሚጀምር ነው። ስለዚህ ይኸንን በሚገባ ለማበሰርና ለመኖር አንድ ልዩ የምህረት ዓመት እርሱም የእግዚአብሔር ምህረት ማእከል ያደረገ ቅዱስ ዓመት አውጂያለሁ እንዳሉ የቅድስት መንበር መግለጫ አስታወቀ።

“ቤተክርስትያን የምንቀበለዉ ለክርስቶስ ስንል ነው”።

$
0
0

(ከአባ ራኔሪዮ ካንታላሜሳ አድሪያና ሜሶቲ እንደተጠናከረችዉ)

የሁለተኛ የቫቲካን ጉባሄ ሰነድ ሉሜን ጀንሲዉም ዎይም ባማረኛ በግርድፉ ስትርጎም የሕዝብ ብራሃን እንደ ሚያስረዳዉ “ቤቴክሪስቲያን የክርስቶስ አካል እና ሙሽራ ናት ይላል”። በሓጥያተኞች የተሞላች ቤተክርስቲያንን መቀበል ማለት ክርስቶስ እራሱን መቀበል ማለት ነዉ። ምክንያቱም ክርስቶስ የህዝብ ሁሉ ብርሃን ነው የሚለዉ የሉሜን ጀንሲዉም ሰነድ በሚገባ እንደ ሚያስረዳዉ ክርስቶስ የቤቴክርስቲያን ማዐዘን በመሆኑ ምንም እንኳዋን ቤቴክርስቲያን በብዙ ህጥያተኛ መሪዎች የተሞላች ብትሆንም ቤቴክርስቲያንን የምንቀበለዉ ክርስቶስ ቤቴክርስቲያንን ስለዎደዳ ቢቻ ሳይሆን እኛ ክርስቶስን ስለምንወደዉም ጭምር ሊሆን ይገባል ሲሉ አክለዋል።

ዋናው ጥያቄ ሊሆን የሚገባዉ ”ቤቴክርስቲያን ምንድናት”? የሚለዉ ሳይሆን ”ቤቴክርስቲያን ማናት” ? ­የሚለዉ ነዉ መሆን ያለበት ካሉ ቡሃላ አባ ካንታላሜሳ መጸሓፍ ቅዱሳችን እንደሚያሳየዉ፣ ”ቤቴክርስቲያን እንከን የለለባት የክርስቶስ ሙሽራ ናት…እርሱም በጣም ስለዎደዳት እራሱን አሳልፎ በመስጠት አነጻት” ይለናል ስለዚህ ቤቴክርስቲያን የክርስቶስ አካል ናት ማለት ነዉ ብለዋል።

አባ ካንታላሜሳ የካርዲናል ራዚንገርን ህሳብ በመጥቀስ ሓሳባቸዉን ስያጠናክሩ ቤቴክርስቲያን የክርስቶስ ሙሽራ በመሆኗ የክርስቶስ አካል ተደርጋ ትቆተራለችኦ ስለዚህም ሙሽራ የሚለዉ ቃል ሊፈጥጸም የሚችለዉ ሁለት ስጋ እና ነፍስ ባላቸዉ ዎንድ እና ሴት መካከል በመሆኑ እነሱም አንድ አካለ ሆነዉ በጋቢቻ እንደሚዋአዱ ሁሉ እንዲሁም የክርስቶስን ስጋ የሚመገቡ ሁሉ ከእርሱ ጋር አንድ አካል ይሆናሉ።

 ስለዚህ ያለቤቴክሪስቲያን እና ያለቅዱስ ቁርባን ክርስቶስ በዓለም ዉስጥ ”አካል ” ሊኖረዉ አይችልም። መማከልም ስጠቅሱ አንድ የዎንጌል ሰባኪ “ቤቴክርስቲያን የክርስቶስ አካል እና ሙሽራ መሆኗ፣ ለአንድ ክርስቲያን መንፈውሳዊ ሕይዎት ምን ዓይንት ትርጉም ሊኖረዉ ይችላል”? ብሎ ያስብ ነበር። ሲመልስም “ቤቴክርስቲያን የክርስቶስ የቅርብ አካሉ መሆኗን ካመንኩኝ፣ እኔ እንደምረዳዉ ቤተክርስቲያን እንደ ቤቴክርስቲያኒነቷ በሓሳብ ደርጃ ቢቻ ሳይሆን በተግባር እኔም የክርስቶስ አካል እንድሆን ታደርገኛለች ማለት ነዉ” ሲል ያስረዳል። ስለዚህ እኔ ቢቻየን ሳይሆን የምኖረዉ ክርስቶስም በኔ ይኖራል ማለት ነው። ይህም እውነታ በተቅበለነዉ ጥምቀት እና በየጊዜዉ በምንቀበልዉ ቅዱስ ቁርባን እዉን ይሆናል ማለት ነዉ።

ቅዱስ ቁርባን እያንዳንዳችንን የክርስቶስ አካል ማለትም ቤቴክርስቲያን እንዲኒሆን ያደርገና። ይህም እኛ ሁለት ባህሪ አንደኛዉ የራሳችን የተፈጥሮ ባህሪ ሁለተኛዉ ገግሞ የክርስቶስን ባህሪ በመላበስ አንድ አካል ቢቻ እንድንሆን ያደርገናል። ከሁለት ባሕሪ ወደ አንድ ባሕሪ እንቀየራለን ማለት ነዉ።

ስለዚህም ታላቁን ሚስጢር የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋዉንና ደሙን ስንቀበል የኛ ተፈጥሮአዊ ባሕሪ በክርስቶስ ይሞላል ሓዋሪያዉ ጳዉሎስ እንድሚለዉ “እኔ ሳልሆን የምኖረዉ ክርስቶስ በኔ ይኖራል” ማለት ነዉ።

እኛ የክርስቶስን ሥጋ እና ደም እንደምንቀበል፣ ክርስቶስም ደግሞ የኛን ሥጋ እና ደም ይረከብና የራሱ ያደርጋል። ስለዚህ ሁለንተናችን የራሳችን መሆኑ ይቀርና የክርስቶስ ይሆናል። ክርስቶስ የኛ እኛ ደግሞ የክርስቶስ እንሆናለን። ስለዚ ሁለንተናችን የክርስቶስ ይሆናል ማለት ነዉ።

በጥምቀት የክርስቶስ የሆንን ሁላችን በተለይም ደግሞ ለሱ አገልግሎት የተቀደሱ ሰዎች በሙሉ ከፍተኛ የሆነ አላፊነት አለብን። ይህ የክርስቶስ አካል ያደረገን ታላቅ አላፊነት ደግሞ የክርስቶስ አካል የሆነችዉን ቤቴክርስቲያን እንዳናዋርድ እና እንዳናቆሽሽ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል።

በመጨረሻም ይህንን የተሰጠንን ታላቅ ሓላፊነት በአግባቡ መዎጣት እንድንችል የክርስቶስ እገዛ ስለምያስፈልገን እርእሰ ሊቃነ ፓፓስ አቡነ ፍራንሲስ እንዳሉት “ከክርስቶስ ጋር እለታዊ የሆነ ግንኙነት” ማድረግ አስፈላጊነቱ አያጠራጥርም።

ባጠቃላይ በቤቴክርስቲያን ሚስጢር መሳተፍ ቢቻ የጎላ መንፈሳዊ በረከትን እና ለዉጥ ለኛ ሊያመጣ  አይችልም። ይልቁንም ክርስትናችንን ክርስቶስ በሚፈልገዉ መልኩ መኖር አስፈላጊ እና ለህይዎታችንም ጠቃሚ እና በረከትን የምያስገኘ ነዉ ሲሉ ሓሳባቸዉን ቋጭተዋል አባ ካንታላሜሳ አድሪያና ሜሶቲ እንደተጠናከረችዉ።

 


የምህረት ዓመት ምክንያት በኢጣሊያ የቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. የሓውፆተ ኖልዎ መርኃ ግብር መሸጋገር

$
0
0

እ.ኤ.አ. ታህሳስ 10 ቀን 2015 ዓ.ም. በኢጣሊያ የሚላኖ ሰበካ ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ካርዲናል አንጀሎ ስኮላ እ.ኤ.አ. ታህሳስ 8 ቀን 2015 ዓ.ም. በተገባው ኢዮቤልዩ ቅዱስ የምህረት ዓመት ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ባላቸው የሐዋርያዊ መርሃ ግብር መጨናነቅ ምክንያት ከቅድስት መንበር ዋና ጸሓፊ ቢሮ የተሰጣቸው መግለጫ ጠቅሰው፣ ቅዱስ አባታችን  እ.ኤ.አ. ግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ.ም. በሚላኖ ሊያካሂዱት ታቅዶ የነበረው የሐውፆተ ኖልዎ መርሃ ግብር ወደ 2017 ዓ.ም. መሸጋገሩ በይፋ ማሳወቃቸው የሚላኖ ሰበካ የዜናና ኅትመት ቢሮ ካሰራጨው መግለጫ ለመረዳት ተችለዋል።

ዜና ዕረፍት

$
0
0

በቦሊቪያ የሳንታ ክሩዝ ደ ላ ሲየራ ሰበካ ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ካርዲናል ኹልዮ ተራዛስ ሳንዶቫል እ.ኤ.አ. ታህሳስ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በ 79 ዓመት ዕድሜያቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው የቦሊቪያ ሰበካ መግለጫ ሲያመልክት፣ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ለሳንታ ክሩዝ ደ ላ ሲየራ ሰበካ ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ሰርጆ አልፍረዶ ጉኣልበርቲ ካላንድሪና የቴሌግራም የሐዘን መግለጫ መልእክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስ አባታችን ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልእክት፦ በእምነት ብርሃንና በተስፋ ኃይል ለተቀበሉት ጥሪ ታማኝ በመሆን በቸርነትና በብርታት ሕይወታቸውን ለወንጌል ለፍትሕና ለሰላም አገልግሎት ያዋሉ በማለት እንደገለጡዋቸው ያመለከተው የቅድስት መንበር መግለጫ አክሎ፦ ነፍሰ ኄር ብፁዕ ካርዲናል ኹልዮ ተራዛስ ሳንዶቫል እ.ኤ.አ. መጋቢት 1936 ዓ.ም. በቫለግራንደ ክፍለ ሃገር የተወለዱና መላ ሕይወታቸው ስለ ድኾች በመጣበቅ የኖሩ ላልተመቻቸለት ድኻው የአገሪቱ ሕዝብ በተለያየ መስክ የሚበጀው አገልግሎት በማቅረብና በማስተባበር የተጉ በአገሪቱ ታሪክ ውስጥ ሁለተኛ ብፁዕ ካርዲናል መሆናቸው ያስታውቃል።

የቅዱሰ ቅዱሳት መድኃኔዓለም ማኅበር አባል እ.ኤ.አ. ሐምሌ 29 ቀን 1962 ዓ.ም. የክህነት ማዕርግ ተቀብለው በቫለግራንደ ክልል የማኅበሩ ቤት አለቃ ከዛም በ 1978 ዓ.ም. በላ ፓዝ ሰበካ ረዳት ጳጳስ በመሆን በማገልገል ላይ እያሉ እ.ኤ.አ.  በ 1982 ዓ.ም. ጳጳስ እንዲሆኑ ተሰይመው በ 1991 ዓ.ም. የሳንታ ክሩስ ደ ላ ሲየራ ሊቀ ጳጳስ የቦሊቪያ ብፁዓን ጳጳሳት ምክር ቤት ለረዥም ዓመታት ሊቀ መንበር በመሆን እንዲሁም ቸላም በሚል አሕጽሮት አቃል ለሚታወቀው ለመላ ላቲን አመሪካና ካሪቢያን ብፁዓን ጳጳሳት ምክር ቤት የዓለማውያን ምእመናን ጉዳይ ለሚከታተለው ድርገት ሊቀ መንበር በመሆን ያገለገሉ፣ በቦሊቪያ የውፉይ ሕይወት ጥሪ ያነቃቁ እ.ኤ.አ. በ 2001 ዓ.ም. በቅዱስ ዮሓንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ብፁዕ ካርዲናል የተሰየሙ መሆናቸው የቅድስት መንበር መግለጫ ገልጦ፣ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በቦሊቪያ ባካሄዱት ዓለም አቀፋዊ ሐዋርያዊ ዑደት ወቅትም ነፍሴ ኄር ብፁዕ ካርዲናል ለሕክምና ይገኙበት ወደ ነበረው ሕክምና ቤት በመሄድ እንደጐበኙዋቸው በማስታወስ ጠቅሶታል።

ማእከላዊት ረፓብሊክ አፍሪቃ፦ ሰላም በማነቃቃቱ ረገድ የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን አስተዋጽዖ

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በማእከላዊት ረፓብሊክ አፍሪቃ ያካሄዱት ዓለም አቀፋዊ ሐዋርያዊ ጉብኝት በማስመልከት የባንጉይ ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ዲየውዶነ ንዛፓላኢንጋ ቅዱስ አባታችን እንደ መንፈሳዊ ነጋዲ ማእከላዊት አፍሪቃን በመጎብኘት ሁሉንም የአገሪቱ ዜጋ ለሰላም አነቃቅተዋል። ካሁን በኋላ የቀረው የገሪቱ ዜጋ በገዛ አገሩ የሰላም ነጋዲ የመሆን ቁርጥ ፍቃድ ነው እንዳሉ ፊደስ የዜና አገልግሎት አስታወቀ።

ብፁዕነታቸው የቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በማእከላዊት ሪፕበሊክ አፍሪቃ ዓለም አቀፋዊ ሐዋርያዊ ጉብኝት ባካሄዱት ቀቅት ያስደመጡት ምዕዳን የለገሱት ስብከት ባካሄዱዋቸው ግኑኝነቶች ያስደመጡት ንግግር በጠቅላላ ክንዋኔው ሰላም ማእከል ያደረገና ሁሉም የሰላም መሣሪያ እንዲሆን ያነቃቃ መሆኑ ገልጠው፣ የቅዱስ አባታችን ምዕዳን በመከተልም በአገሪቱ ሊካሄድ በተቃረበው ሕዝባዊ ምርጫ የቀድሞ ርእሰ ብሔር ፍራንሱዋ ቦዚዘ በእጩነት ለምርጫ እንዳይሳተፉ የተላለፈው ውሳኔ በመቃወም ባንጉይ በሚገኘው የምስልምና ሃይማኖ ተከታይ በብዛት በሚኖርበት ፒከይፋይፍ ሰፈር የተቀሰቀሰው ግጭት እዲወገድና ሰላም ለማነቃቃት ወደዚያ ክልል ወጣቶችን በማስከተል መሄዳቸው ፊደስ የዜና አገልግሎት ይጠቁማል።

ብፁዕ አቡነ ንዛፓላይንጋ በሙስሊሞች ክልል የሰላም መልእክተኛ

እ.ኤ.አ. ታህሳስ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. ብፁዕነታቸው በእግራቸው በዚያ ውጥረት በሚታይበት ሰፈር ከወጣቶች ጋር የሰላም ጉዞ በሚል ስያሜ በመዘዋወር ከሁሉም ነዋሪዎች ጋር በመገናኘት አንተ እኔ የሚለው ለግጭት የሚገፋፋው ለያይ አጥር እንዲፈርስ ሁሉም የሰላም መሣሪያ ሆኖ እንዲገኝ ጥሪ አቅርበዋል። እርስ በእርስ መከባበርና መቀባበል ያለው አስፈላጊነት በመመስከር በተለይ ደግሞ ለሰላማዊ ማኅበራዊ ኑሮ ይቀር መባባል መማማር እርቅ ለሰላም ወሳኝ መሆኑ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. በባንጉይ ለምህረት ዓመት ቅዱስ በር በመክፈት በለገሱት ስብከት ያሰመሩበት ቃል ያስተጋባ የሰላም ጉዞ ነበር እንዳሉ ፊደስ የዜና አገልግሎት አስታወቀ።

በቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. አማካኝነት የተጸገወው መልካም መንፈስ በአገሪቱ እያስተነፈሰ ነው

ቅዱስ አባታችን ያካሄዱት ጉብኝት የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ምእመናንና ማኅበረ ክርስቲያንን ብቻ ሳይሆን እንዳውም የምስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ቅዱስነታቸው ሲጎበኙን እንዴት መታደል ነው በማለት ሰላም እንጂ ጦርነትን አንፈልግም ሲሉ አቅርበዉት በነበረው የሰላም ጥሪ ድምጻቸውን በማስተባበር እያስተጋቡ ነው። የፒከይፋይፍ ሰፈር ነዋሪ ወጣቶች ከወጣት ክርስቲያኖች ወንድሞቻቸው ጋር በመገናኘት ስለ ሰላም እያካሄዱት ያለው ቅስቀሳ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. በአገሪቱ የለገሱት መንፈስ በሁሉም ዜጋ ልብና በአገሪቱ ጭምር እያስተነፈሰ ነው እንዳሉ ፊደስ የዜና አገልግሎት ካሰራጨው ዜና ለመረዳት ተችለዋል።

ኖስትራ አሄታቴ (ያለንበት ዘመን)፣ ከአይሁዳዊያን ጋር ያለንን ግንኙነት እና ልዩነት የሚገልጽ የይሁለተኛ የቫቲካን ጉባሄ ሰነድ

$
0
0

በብጹዕ ካርዲናል ኩርት ኮክ በጂህዳ አኩሊኖ እንደተዘጋጀ

የዚህ ጹሁፍ ሃሳብ ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ከሁለተኛ የቫቲካን ጉባሄ ቡሃላ በአይሁድ እና በካቶሊክ ማህበረሰብ መካከል ስለተደርጉት ዉይይቶች እና ስለተገኘዉ ፍሬያማ ለዉጥ ለማንሳት በማሰብ ነዉ። በተለይም ደግሞ በዚህ ሰነድ በአራተኛ አንቀጽ የተጠቀሰው ፍሬ ሓሳብ ስለካቶሊክ እና አይሁዳዊያን ግንኙነት የሚገልጽ ቢቻ ሳይሆን ከተለያዩ እመነቶች ጋር ያለንን ግንኙነትንም በጣም እንዲጠናከር ያገዘም ጭምር ነው። መሪ ሃሳቡም ከአይሁድ ማህበረሰብ ጋር ልኖረን ስለሚገባ አድስ መንፈሳዊ አካሄድ የምያስረዳ ነዉ።

በዚህ አንጻር የካቶሊክ ቤተክርስትያን ከአይሁዳዊያን ጋር የምታደርገዉ ግንኙነት ከሌሎች እምነቶች ጋር ለምታደርገዉ ዉይይት እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ሊይገልግል ስለምችል በጥንቃቄና በትኩረት ልታይ ይገባዋል።

በምደረገዉ መንፍሳዊ የመግባባት ዉይይት ላይ ትኩረት ወይም ልሰመርባቸዉ ይሚገባቸዉ ጉዳዮች፣ ለምሳሌም የራዕይን አስፈላጊነት፤ በብሉይ እና በአዲስ ኪዳን መካከል ያለዉ በፍጹም ልለያይ የማይችል ግንኙት፤ የእየሱስ የዓለም ሁሉ አዳኝ መሆኑን የሚገልጽ እምነት፤ እግዝሓብሄር ለእስራኤል ሕዝብ የገባዉ ቃል ኪዳን የማይሻር መሆኑንና ዓለማቀፋዊ የቤተክርስትያን የወንጌለ ስብክት አገልግሎት ትኩረት ሊሰጥባቸዉ የሚገባቸዉ ጉዳዮች ናቸዉ።

ኖስትራ አሄታቴ (ያለንበት ዘመን)፣ በካቶሊክ እና በአይሁዳዊያን መካከል የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖር እና እንዲፈጠር ያስቻለ ሰነድ ቢቻ ሳይሆን እንደ ጠላት የሚፈራረጁ ሁለቱ ማሕበረሰቦች በመቀራረብ እንድሰሩ እና ግጭቶችን በመነጋገርና አግባብ ባለዉ መልኩ መፍታት እንዲችሉ ያስቻለም ጭምር በመሆኑ አስፈላግነቱ በጣመ የጎላ ነዉ። ይህንን መነሻ በማድረግ እ.አ.አ 1974 ዕርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ፓዉሎስ ስድስተኛ ከአይሁድ ማህበረሰብ ጋር የምደረዉን ዉይይት በተጠናከረ መልኩ ለማስኬድ በማሰብ ኮሚቴ በማቋቋም ዉይይቱ በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀጥል በማድረጋቸዉ እንደ አብነት ስቆጠሩ፣የሳቸዉን አራዐያ በመከተል ቀጣዮቹ ጳጳሳትም አሁን እሳካሉት ቅዱስ አባታችን ፍራንሲስም የተልዕኮዋቸው አንዱ ሥራ አድርገዉ በተጠናከር መልኩ ሥራዉን አስቀጥለዉ ሰንብተዉአል።

በሌላም በኩል ስታይ አይሁዳዊያን እና ክርስቲያኖች አንዱ አንዱን ልያበለጽግ የሚችል ሀብት ስላላቸው፣ ከሌላዉ እምነት በተሻለ አይሁዳዊያን እና ክርስቲያኖች የምያስተሳስራቸዉ ነገር ስለሚበዛ በተለይም ደግሞ ክርስትና ከአይሁዳዊያን የሚመዘዝ የዘር ግንድ ሰላለው ግንኙነቱ ከለላዉ እምነት በተሻለ የተቆራኘ እና የተሳሰረ ነው። ያለ አይሁዳዊያን ቤተክርስቲያን የደህንነት ታሪኳን የሚገልጸዉን እና ከአይሁድ የሚመዘዘዉን ማንንነቷን ታጣለች ማለት ነዉ።

በአብዛኛዉ ከአይሁድ ጋር የሚደረገዉ ዉይይት ፍሬያማ የሚሆንበት ምክንያት የሁለቱን ሃይማኖቶች ማንነት የሚያገናኝ እና በጥብቅ የምያስተሳስራቸዉ ታሪክ በመኖሩ ምክንያት ጭምር ነው። ሁለቱንም በይበልጥ የምያስተሳስራቸዉ ጉዳይ ቢኖር እየሱስ አይሁዳዊ መሆኑና በአይሁደ ጊዜ መኖሩ ስሆን የሚያለያያቸዉ ደግሞ በእየሱስ አዳኝነት ላይ የሚያነሱት ጥያቄዎች ናቸው።

እየሱስ የዓለም ሁሉ አዳኝና አማላጅ መሆኑን፣ ሓዋርያዉ ጳዉሎስ እንዳስቀመጠዉ የማይለወጥ እና የማይሻር ሀቅ ነዉ። በአንጻሩ ደግሞ አይሁዳዊያን መንፈሳዊ ጸጋን እና በረከትን የምያገኙት በቀጥታ ከእግዝሓብሔር ዘንድ ቢቻ ነዉ። ትልቁ ትኩረት ልሰጠዉ የሚገባዉ ጉዳይ ታድያ አይሁዳዊያን ጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሳያምኑ እንደት ልድኑ ይችላሉ የሚለዉ ስሆን፣ የኖስትራ አሄታቴ (ያለንበት ዘመን)፣  ዶክመንት ስመልስም “ለማብራራት የምያዳግት መለኮታዊ ሚስጢር ነዉ” ብሎ ይደመድማል። 

ቤተክርስትያን ወደ አይሁዳዊያን የምታደርገዉ መንፈሳዊ ተዕልኮ በይዘቱ ቀላል ቢመስልም እዉነታዉ የምያሳየዉ ግን በጣም ጥንቃቄ ልቸረዉ የሚገባው አስቸጋሪ ተልዕኮ እና እሾህ የበዛበት አስቸጋሪ መንገድ መሆኑን ያሳያል ምክንያቱም ከመኖር ህልዉናቸው ጋር የተያያዘ በመሆኑ።

ስለዚህም ቤተክርስትያን ልትረዳዉ የሚገባዉ ነገር ቢኖር በአንድ አምላክ በምያምኑ ወደ አይሁዳዊያን የምደረገዉ መንፈሳዊ ተልዕኮ ከለሎች ክርስትያን ካልሆኑና የራሳቸዉ ፍልስፍና ካላቸዉ እምነቶች ለየት ያለ መሆኑን በመረዳት መረዳት ይጠበቅባታል።

የካቶሊክ ቤተክርስትያን ማንኛውንም አይነት መንፈሳዊ ተልዕኮ ወደ አይሁድ ምድር ለማድረግ አትነሳሳም፣ ነገር ግን ክርስትያኖች ክርስቶስን በሕይዎታቸዉ በአይሁድ ማህበረሰብ ፊት በትህትና እና በጥንቃቄ፣ በተጨማሪም አይሁዳዊያን የእግዚሓብሄርን ቃል እንደምያዉቁ ከግምት ዉስጥ በማስገባት በተግባር እንድመሰክሩ ግን ታበረታታለች።

በመጨረሻም የኖስትራ አሄታቴ ሰነድ የምያጠቃልለዉ ሁለቱም አይማኖቶች በጋራ ያላቸዉን መልካም የሆኑና ለዓለማችን አስፍላጊ የሆኑ እንደ ፍትህ፣ ሰላም እና አንድነትን በማረጋገጥ በዓለም ላይ እርቅንና ሰላምን ላማስፈን መጣር ይኖርባቸዋል፣ መክንያቱም የዓለም ሰላም ልጠናከርና ልረጋገጥ የምችለዉ በሀይማኖቶች መካከል ጥብቅ የሆነ ዉይይት ስደረግ ቢቻ መሆኑም ያስረዳል።

 

ኖስትራ አሄታቴ (ያለንበት ዘመን)፣ ከአይሁዳዊያን ጋር ያለንን ግንኙነት እና ልዩነት የሚገልጽ የሁለተኛ የቫቲካን ጉባሄ ሰነድ

$
0
0

በብጹዕ ካርዲናል ኩርት ኮክ በጂህዳ አኩሊኖ እንደተዘጋጀ

የዚህ ጹሁፍ ሃሳብ ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ከሁለተኛ የቫቲካን ጉባሄ ቡሃላ በአይሁድ እና በካቶሊክ ማህበረሰብ መካከል ስለተደርጉት ዉይይቶች እና ስለተገኘዉ ፍሬያማ ለዉጥ ለማንሳት በማሰብ ነዉ። በተለይም ደግሞ በዚህ ሰነድ በአራተኛ አንቀጽ የተጠቀሰው ፍሬ ሓሳብ ስለካቶሊክ እና አይሁዳዊያን ግንኙነት የሚገልጽ ቢቻ ሳይሆን ከተለያዩ እመነቶች ጋር ያለንን ግንኙነትንም በጣም እንዲጠናከር ያገዘም ጭምር ነው። መሪ ሃሳቡም ከአይሁድ ማህበረሰብ ጋር ልኖረን ስለሚገባ አድስ መንፈሳዊ አካሄድ የምያስረዳ ነዉ።

በዚህ አንጻር የካቶሊክ ቤተክርስትያን ከአይሁዳዊያን ጋር የምታደርገዉ ግንኙነት ከሌሎች እምነቶች ጋር ለምታደርገዉ ዉይይት እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ሊይገልግል ስለምችል በጥንቃቄና በትኩረት ልታይ ይገባዋል።

በምደረገዉ መንፍሳዊ የመግባባት ዉይይት ላይ ትኩረት ወይም ልሰመርባቸዉ ይሚገባቸዉ ጉዳዮች፣ ለምሳሌም የራዕይን አስፈላጊነት፤ በብሉይ እና በአዲስ ኪዳን መካከል ያለዉ በፍጹም ልለያይ የማይችል ግንኙት፤ የእየሱስ የዓለም ሁሉ አዳኝ መሆኑን የሚገልጽ እምነት፤ እግዝሓብሄር ለእስራኤል ሕዝብ የገባዉ ቃል ኪዳን የማይሻር መሆኑንና ዓለማቀፋዊ የቤተክርስትያን የወንጌለ ስብክት አገልግሎት ትኩረት ሊሰጥባቸዉ የሚገባቸዉ ጉዳዮች ናቸዉ።

ኖስትራ አሄታቴ (ያለንበት ዘመን)፣ በካቶሊክ እና በአይሁዳዊያን መካከል የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖር እና እንዲፈጠር ያስቻለ ሰነድ ቢቻ ሳይሆን እንደ ጠላት የሚፈራረጁ ሁለቱ ማሕበረሰቦች በመቀራረብ እንድሰሩ እና ግጭቶችን በመነጋገርና አግባብ ባለዉ መልኩ መፍታት እንዲችሉ ያስቻለም ጭምር በመሆኑ አስፈላግነቱ በጣመ የጎላ ነዉ። ይህንን መነሻ በማድረግ እ.አ.አ 1974 ዕርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ፓዉሎስ ስድስተኛ ከአይሁድ ማህበረሰብ ጋር የምደረዉን ዉይይት በተጠናከረ መልኩ ለማስኬድ በማሰብ ኮሚቴ በማቋቋም ዉይይቱ በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀጥል በማድረጋቸዉ እንደ አብነት ስቆጠሩ፣የሳቸዉን አራዐያ በመከተል ቀጣዮቹ ጳጳሳትም አሁን እሳካሉት ቅዱስ አባታችን ፍራንሲስም የተልዕኮዋቸው አንዱ ሥራ አድርገዉ በተጠናከር መልኩ ሥራዉን አስቀጥለዉ ሰንብተዉአል።

በሌላም በኩል ስታይ አይሁዳዊያን እና ክርስቲያኖች አንዱ አንዱን ልያበለጽግ የሚችል ሀብት ስላላቸው፣ ከሌላዉ እምነት በተሻለ አይሁዳዊያን እና ክርስቲያኖች የምያስተሳስራቸዉ ነገር ስለሚበዛ በተለይም ደግሞ ክርስትና ከአይሁዳዊያን የሚመዘዝ የዘር ግንድ ሰላለው ግንኙነቱ ከለላዉ እምነት በተሻለ የተቆራኘ እና የተሳሰረ ነው። ያለ አይሁዳዊያን ቤተክርስቲያን የደህንነት ታሪኳን የሚገልጸዉን እና ከአይሁድ የሚመዘዘዉን ማንንነቷን ታጣለች ማለት ነዉ።

በአብዛኛዉ ከአይሁድ ጋር የሚደረገዉ ዉይይት ፍሬያማ የሚሆንበት ምክንያት የሁለቱን ሃይማኖቶች ማንነት የሚያገናኝ እና በጥብቅ የምያስተሳስራቸዉ ታሪክ በመኖሩ ምክንያት ጭምር ነው። ሁለቱንም በይበልጥ የምያስተሳስራቸዉ ጉዳይ ቢኖር እየሱስ አይሁዳዊ መሆኑና በአይሁደ ጊዜ መኖሩ ስሆን የሚያለያያቸዉ ደግሞ በእየሱስ አዳኝነት ላይ የሚያነሱት ጥያቄዎች ናቸው።

እየሱስ የዓለም ሁሉ አዳኝና አማላጅ መሆኑን፣ ሓዋርያዉ ጳዉሎስ እንዳስቀመጠዉ የማይለወጥ እና የማይሻር ሀቅ ነዉ። በአንጻሩ ደግሞ አይሁዳዊያን መንፈሳዊ ጸጋን እና በረከትን የምያገኙት በቀጥታ ከእግዝሓብሔር ዘንድ ቢቻ ነዉ። ትልቁ ትኩረት ልሰጠዉ የሚገባዉ ጉዳይ ታድያ አይሁዳዊያን ጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሳያምኑ እንደት ልድኑ ይችላሉ የሚለዉ ስሆን፣ የኖስትራ አሄታቴ (ያለንበት ዘመን)፣  ዶክመንት ስመልስም “ለማብራራት የምያዳግት መለኮታዊ ሚስጢር ነዉ” ብሎ ይደመድማል። 

ቤተክርስትያን ወደ አይሁዳዊያን የምታደርገዉ መንፈሳዊ ተዕልኮ በይዘቱ ቀላል ቢመስልም እዉነታዉ የምያሳየዉ ግን በጣም ጥንቃቄ ልቸረዉ የሚገባው አስቸጋሪ ተልዕኮ እና እሾህ የበዛበት አስቸጋሪ መንገድ መሆኑን ያሳያል ምክንያቱም ከመኖር ህልዉናቸው ጋር የተያያዘ በመሆኑ።

ስለዚህም ቤተክርስትያን ልትረዳዉ የሚገባዉ ነገር ቢኖር በአንድ አምላክ በምያምኑ ወደ አይሁዳዊያን የምደረገዉ መንፈሳዊ ተልዕኮ ከለሎች ክርስትያን ካልሆኑና የራሳቸዉ ፍልስፍና ካላቸዉ እምነቶች ለየት ያለ መሆኑን በመረዳት መረዳት ይጠበቅባታል።

የካቶሊክ ቤተክርስትያን ማንኛውንም አይነት መንፈሳዊ ተልዕኮ ወደ አይሁድ ምድር ለማድረግ አትነሳሳም፣ ነገር ግን ክርስትያኖች ክርስቶስን በሕይዎታቸዉ በአይሁድ ማህበረሰብ ፊት በትህትና እና በጥንቃቄ፣ በተጨማሪም አይሁዳዊያን የእግዚሓብሄርን ቃል እንደምያዉቁ ከግምት ዉስጥ በማስገባት በተግባር እንድመሰክሩ ግን ታበረታታለች።

በመጨረሻም የኖስትራ አሄታቴ ሰነድ የምያጠቃልለዉ ሁለቱም አይማኖቶች በጋራ ያላቸዉን መልካም የሆኑና ለዓለማችን አስፍላጊ የሆኑ እንደ ፍትህ፣ ሰላም እና አንድነትን በማረጋገጥ በዓለም ላይ እርቅንና ሰላምን ላማስፈን መጣር ይኖርባቸዋል፣ መክንያቱም የዓለም ሰላም ልጠናከርና ልረጋገጥ የምችለዉ በሀይማኖቶች መካከል ጥብቅ የሆነ ዉይይት ስደረግ ቢቻ መሆኑም ያስረዳል።

 

Viewing all 1660 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>