Quantcast
Channel: የቫቲካን ሬድዮ
Viewing all 1660 articles
Browse latest View live

የሐምሌ 30/2009 ዓ.ም. የእለተ ሰንበት ምንባባት እና አስተንትኖ በአባ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ

$
0
0

የሐምሌ 30/2009 ዓ.ም. የእለተ ሰንበት ምንባባት እና አስተንትኖ

የእለቱ ምንባባት

  1.  ቲቶ 3:1-15 በጎ የሆነውን ማድረግ

    ሰዎች ለገዦችና ለባለ ሥልጣናት እንዲገዙ፣ እንዲታዘዙና መልካም የሆነውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስባቸው። እንዲሁም በማንም ላይ ክፉ እንዳይናገሩ፣ ሰላማውያን እንዲሆኑ፣ ለሰዎችም ሁሉ ከልብ የመነጨ ትሕትና እንዲያሳዩ አስገንዝባቸው።

    ቀደም ሲል እኛ ራሳችን ማስተዋል የጐደለን፣ የማንታዘዝ፣ የተታለልን፣ ለተለያየ ምኞትና ምቾት ባሪያ ሆነን የተገዛን ነበርን፤ እየተጣላንና እርስ በርስ እየተጠላላን በክፋትና በምቀኝነት እንኖር ነበር። ነገር ግን የአዳኛችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ፍቅር በተገለጠ ጊዜ፣ ስላደረግነው የጽድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ከምሕረቱ የተነሣ አዳነን። ያዳነንም ዳግም ልደት በሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታደስ ነው፤ ይህንም መንፈስ እግዚአብሔር በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእኛ ላይ አትረፍርፎ አፈሰሰው፤ ይኸውም በጸጋው ጸድቀን የዘላለምን ሕይወት ተስፋ ይዘን ወራሾች እንድንሆን ነው። ይህም የታመነ ቃል ነው። በእግዚአብሔር ያመኑቱ መልካሙን ነገር ለማድረግ ራሳቸውን አሳልፈው ይሰጡ ዘንድ እነዚህን ነገሮች አስረግጠህ እንድትናገር እፈልጋለሁ። ይህ መልካምና ለማንኛውም ሰው የሚጠቅም ነው።

    ነገር ግን ከንቱ ከሆነ ክርክርና ከትውልድ ሐረግ ቈጠራ፣ ከጭቅጭቅና ስለ ሕግ ከሚነሣ ጠብ ራቅ፤ ይህ ዋጋ ቢስና ከንቱ ነውና። መከፋፈል የሚያመጣን ሰው አንድ ጊዜ ምከረው፤ ለሁለተኛ ጊዜ አስጠንቅቀው፤ ከዚያ ካለፈ ከእርሱ ጋር አንዳች ነገር አይኑርህ። እንዲህ ዐይነቱ ሰው የሳተና ኀጢአተኛ ነው፤ ራሱንም እንደሚኰንን ዕወቅ።

  2. ለእግዚአብሔር መኖር 1 ጴጥሮስ 4:6-11 ይህን በመሰለ ብኩን ሕይወት ከእነርሱ ጋር ስለማትሮጡ እንግዳ ሆኖባቸው በመደነቅ ይሰድቧችኋል። ነገር ግን በሕያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ ለተዘጋጀው መልስ ይሰጣሉ። ወንጌል ለሙታን እንኳ ሳይቀር የተሰበከው በዚህ ምክንያት ነው፤ ስለዚህ እንደ ማንኛውም ሰው በሥጋ ይፈረድባቸዋል፤ በመንፈስ ግን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ይኖራሉ።

የዚህን አስተንትኖ ሙሉ ይዘት ከዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!

 

የሁሉ ነገር መጨረሻ ተቃርቦአል፤ ስለዚህ መጸለይ እንድትችሉ ንቁ አእምሮ ይኑራችሁ፤ ራሳችሁንም የምትገዙ ሁኑ። ፍቅር ብዙ ኀጢአትን ይሸፍናልና ከሁሉ በላይ እርስ በርሳችሁ ከልብ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ያለ ማጒረምረም እንግድነት ተቀባበሉ። እንደ ታማኝ የእግዚአብሔር ልዩ ልዩ ጸጋ መጋቢ እያንዳንዱ ሰው በተቀበለው የጸጋ ስጦታ ሌላውን ያገልግል፤ ከእናንተ ማንም የሚናገር ቢኖር እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ የሚያገለግልም ቢኖር እግዚአብሔር በሚሰጠው ብርታት ያገልግል፤ ይኸውም እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እንዲከብር ነው፤ ክብርና ኀይል ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይሁን፤ አሜን።

  1. የማርቆስ ወንጌል 6:47-56

እየሱስ በውሃ ላይ ተራመደ

በመሸም ጊዜ ጀልባዋ ባሕሩ መካከል ነበረች፤ እርሱም ብቻውን በምድር ላይ ነበር። ነፋስ በርትቶባቸው ስለ ነበር፣ ደቀ መዛሙርቱ ከመቅዘፊያው ጋር ሲታገሉ አያቸው፤ በአራተኛውም ክፍለ ሌሊት ገደማ፣ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ እነርሱ መጣ፤ በአጠገባቸውም ዐልፎ ሊሄድ ነበር። ነገር ግን በባሕር ላይ ሲሄድ ባዩት ጊዜ ምትሐት መስሎአቸው ጮኹ፤ ሁሉም እርሱን ባዩት ጊዜ ደንግጠው ነበርና።እርሱም ወዲያውኑ አነጋገራቸውና፣ “አይዞአችሁ እኔ ነኝ፤ አትፍሩ!” አላቸው። እርሱም በጀልባዋ ላይ ወጥቶ አብሮአቸው ሆነ፤ ነፋሱም ተወ፤ እነርሱም እጅግ ተደነቁ፤ የእንጀራውን ታምር አላስተዋሉም ነበርና፤ ልባቸውም ደንድኖ ነበር።በተሻገሩም ጊዜ፣ ጌንሴሬጥ ደርሰው ወረዱ፤ ጀልባዋንም እዚያው አቆሙ። ወዲያው እንደ ወረዱም፣ ሕዝቡ ኢየሱስን ዐወቁት፤ ወደ አካባቢውም ሁሉ በመሮጥ ሕመምተኞችን በዐልጋ ላይ እየተሸከሙ እርሱ ወደሚገኝበት ስፍራ ሁሉ ያመጡ ነበር። በየደረሰበት መንደር ወይም ከተማ ወይም ገጠር ሁሉ ሕመምተኞችን በየአደባባዩ እያስቀመጡ የልብሱን ጫፍ እንኳ ለመንካት ይለምኑት ነበር፤ የነኩትም ሁሉ ይድኑ ነበር።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንዲሁም በጎ ፈቃድ ያላችሁ ሁሉ

እንደየ ተግባራችን ሳይሆን በምሕረቱና በቸርነቱ ደግፎን በጸጋውና በበረከቱ ሞልቶን፣ ተንከባክቦን ለእዚህች እለት ያደረሰን እግዚኣብሔር አምላካችን ስሙ ለዘልዓለም የተመሰገነ ይሁን።

በዛሬው ቅዱስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ያከናወናቸውን ሦስት ዋና ዋና ተግባሮችን እናገኛለን። በመጀመሪያም ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ተለይቶ ብቻውን ለመጸለይ ወደ ተራራ ወጣቱን የሚያመልክት ሲሆን ይህም እኛም ብንሆን ይህንን የኢየሱስን አራያ በመከትል ለራሳችን ጊዜ በመስጠት በጸጥታ ከእግዚኣብሔር ጋር በመሆን ብቻችንን ከእርሱ ጋር ማውራት መመካከር፣ የልባችንን ማካፈል የመንፈስ ደስታን ይሰጣል፣ ቡራኬንም እንደ ሚያስገኝ አወቀን ለእግዚኣብሔር ጊዜ መስጠት እንደ ሚገባን ያሳስበናል።

በሁለተኛ ደረጃ በዛሬው ቅዱስ ወንጌል ውስጥ  የተገለጸው የእየሱስ ድርጊት “በመሸም ጊዜ ጀልባዋ ባሕሩ መካከል በነበረችበት ወቅት ነፋስ በርትቶባቸው ስለ ነበር፣ ደቀ መዛሙርቱ ከመቅዘፊያው ጋር እየታገሉ በነበሩበት ወቅት ኢየሱስ በባሕር ላይ እየተራመደ ወደ እነርሱ መሚመጣበት ወቅት እረሱ ሌላ መንፈስ መስሎዋቸው ስለነበረ በፍርሃት እየጮኹ በነበሩበት ወቅት “አይዙዋችሁ አትፍሩ” በማለት ወደ ጀልባው ገብቶ ከእነርሱ ጋር በተቀመጠ ጊዜ አውሎንፋሱ ጸጥ እንዳለ የሚገልጽ ነው።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንዲሁም በጎ ፈቃድ ያላችሁ ሁሉ! ዛሬም ቢሆን እየሱስ አይዞአችሁ! እኔ ነኝ አትፍሩ! ይለናል።  

በዛሬው ወንጌል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅ የሆነ የምንፅናናበት ቃል ይናገረናል። በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ ይብዛም ይነስም የየራሳችንን ፍርሐት ወይንም ስጋት አለን፡፡ ይህ ከምን የመነጨ ይሆን? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ስለምን እንዲህ ትፈራላችሁ? እስከዚህ እምነት የላችሁምን ይለናል፡፡ /ማር 4፡4ዐ/ ፍርሃት ምንድን ነው? ፍርሃት በሰው ሕይወት ውስጥ የሚከሰት የድንጋጤ ስሜት ነው፡፡ ይህ ስሜት አእምሮን ሲቆጣጠር ሰው በትክክል ማሰብና መስራት፣ የሚገባውን ማድረግ ወይም መሆን የሚገባውን መሆን ያቅተዋል፡፡ በእርግጥ በአጠቃላይ አነጋገር ሦስት አይነት ፍርሐት አለ፡፡

በሦስተኛ ደረጃ በዛሬው ቅዱስ ወንጌል ውስጥ የተጠቀሰው የእየሱስ ተግባር ደግሞ ባሕሩን በተሻገሩም ጊዜ፣ ወዲያው እንደ ወረዱም፣ ሕዝቡ ኢየሱስን አውቀውት ስለነበር፤ ወደ አካባቢውም ሁሉ በመሮጥ ሕመምተኞችን በአልጋ ላይ እየተሸከሙ እርሱ ወደ ሚገኝበት ስፍራ ሁሉ ያመጡ እንደ ነበረ፣ እነርሱም በየደረሰበት መንደር፣ ከተማና ገጠር ሕመምተኞችን በየአደባባዩ እያስቀመጡ የልብሱን ጫፍ እንኳ ለመንካት ይለምኑት ነበር፤ የነኩትም ሁሉ ይድኑ ነበር የሚለው ነው።

ኢየሱስ ወዲያውኑ ከጀልባው እንደ ወረደ ሕዝቡ ወዲያውኑ አውቁት ይለናል። ማርቆስ በዛሬው ወንጌሉ ከተለያዩ አከባቢዎች የተውጣጡ ብዙ ሕዝቦች ኢየሱስን ፍለጋ እንደ መጡ ይነግረናል። ታዲያ ይህን ያህል ብዙ ሕዝብ ኢየሱስን እንዲከተል ያነሳሳው ጉዳይ ምን ይሆን? ብለን መጠየቅ ተገቢ ይመስለኛል።

በዛሬው ቅዱስ ወንጌል እንደ ተጠቀሰው ይህ ሰፊ የሆነ ሕዝብ ኢየሱስን ፍለጋ የወጣበት ምክንያት ኢየሱስ የሚባለውን የእግዚኣብሔር ልጅ ለማየት ካደረባቸው ጉጉት የተነሳ ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ከሕመማቸውና ከተለዩዩ ደዌዎቻችው ለመፈወስ ስለፈለጉ ጭምር ነው።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ

ታዲያ ዛሬ እኔና እናንተ እየሱስን የምንፈልገው ለምንድነው? ከሕመማችን፣ ከጭንቀታችን፣ ከሽክማችን ወዘተ. . . እንዲያድነን ስለምንፈልግ ነው? ብለን እራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል። ዛሬ የምንኖርበት ዓለማችን በብዙ ነገሮች ተወጥረን እንገኛለን። ታዲያ “አይዙዋችሁ አትፍሩ እኔ ነኝ” የሚለውን እየሱስ፣ በሕይወታችን ውስጥ በእየለቱ የሚነሳውን ማእበል ለማጥፋት ብቃት ያለውን እርሱን፣ በፍርሃት በምንዋጥበት እና የዚህ ዓለም ነገሮች እንደ ማእበል ሆነው ሕይወታችንን በሚያናውጡበት ሰዓት ይህንን የሕይወት ማዕበል “ጽጥ በል” ብሎ ሊያረጋጋን ብቃት ያለውን እየሱስን፣ የሕይወታችን ዋስትና ይሆን ዘንድ እንፈልገዋለን ወይ? መልሱን ለእያንዳዳችሁ እተዋለሁኝ።

እየሱስ የዚህ ምድር ተልዕኮውን በይፋ በጀመረበት ወቅት አገልግሎቱን በስፋት የጀመረው በየመንደሩ እይዞረ በማስተማር፣ በማጽናናት፣ የሞተን በማስነሳት፣ የታመመን በመፈወስ መሆኑን የማርቆስ ወንጌል ያስተምረናል።

ለምሳሌም ጊዜው ደርሶአል፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለች፤ ንስሓ ግቡ፤ በወንጌልም እመኑ” እያለ ከሰበከበት ከገሊላ አንስቶ፣ በቅፍርናሆም  በሰንበት ቀን ወደ ምኵራብ ገብቶ ማስተማር እንደ ጀመረ፣ ወደ በረሃ መሰደዱንና በዚያም ሕዝቡ ሊፈልገው መምጣቱን፣ በባሕር ዳር ቆጭ ብሎ ሕዝቡን ማስተማሩን፣ ከፍተኛ ወደ ሆነ ስፍራ በውጣት በዚያም ሕዝቡን የተራራው ላይ ስብከት ተብሎ ይሚታወቀውን መስበኩን፣ በእየደባባዩ እና በየከተማው እየተዘዋወረ ሕሙማንን መፈወሱን፣ የመሳሰሉትን ነገሮች እየሱስ በመፈጸሙ የተነሳ ከሕዝቡ ዘንድ አድናቆት ተችሮት ነበር። በእነዚህ እና እነዚህን በመሳሰሉት ምክንያቶች ነው እንግዲህ ሕዝቡ ኢየሱስን ለመፈለግ የሚወጣው።

እየሱስ በሕዝቡ የተፈለገበት ዋንኛው ምክንያት እርሱ በሽተኞቻችውን ስለፈወሰ፣ ስላዳቸው፣ ስለአበላቸው ስለአጠጣቸው ብቻ ሳይሆን ይፈልጉት የነበሩት ነገር ግን ከእነዚህ ሥጋዊ ፍልጎቶች ባሻገር በማርቆስ ወንጌል 6:34 ላይ እንደ ተጠቀሰው “ሕዝቡ እረኛ እንደ ሌላቸው በጎች” ተጥለው የነበሩ በመሆናቸው የተነሳ ጭምር ነው። ኢየሱስ ይህንን ታሪክ በመቀየር በየሰፈሮቻቸው፣ በየቄያቸው በየከተሞቻቸው ሳይቀር እየተዘዋወረ ያስተምር ስለነበር ይህ ትሕትናው እና ትጋቱ የሕዝቡን ልብ ቆርቁሮ አነሳስቶም ነበር። የስበከውን በሕይወቱ አሳይቱዋል፣ በሕይወቱ ተጨባጭ በሆነ መልክ የኖረውን ኑሮ በቃላት ስበኮታል። ከዚህም የምንረዳው ማንኛችንም ብንሆን ሰዎችን ወደ እኛ ለመሳብ ከፈለግን፣ የክርስቶስን ቃል በመጽናት መስብክ ከፈለግን፣ ስብከታችን ውጤታማ እና ፍሬያማ መሆን የሚችለው ቃላችን ከተግባራችን፣ ተግባራችን ደግሞ ከቃላችን ጋር የተገጣጠመ ሲሆን ብቻ እንደ ሆነ ከእየሱስ ሕይወት መማር እንችላለን። ስለዚህም በዛሬው እለተ ሰንበት እየሱስ ልባችንን ከማንኛውም ፍርሃት ያላቅቅልን ዘንድ፣ በኑሮዋችን እርሱን በመምሰል በመኖር ለሌሎች በረከት የምኖንበትን ጸጋ ይሰጠን ዘንድ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማሪያም አማላጅነት ልንልምነው ይገባል። የሰማነውን በልቦናችን ያሳድርልን። አሜን!

 

  1. በተፈጥሮ እግዚአብሔር ለሰው የሚሰጠው ፍርሃት፡ ለምሳሌ አደጋን በመፈራት የምንጠነቀቅበት፣ እሳትን ፈርቶ መሸሽ፣ መኪና እንዳይገጨን መሸሽ ወዘተ…
  2. ፈሪሃ እግዚአብሔር፡ ትክክል፤ አስፈላጊ ከማክበር የሚመነጭ ቅዱስ ፍርሃት ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ለመኖር፣ ትዕዛዙን ለመጠበቅ እግዚአብሔርን መፍራት መልካምና ትክክለኛ ነው፡፡ እግዚአብሔርን መፍራት እኛን ከኃጢያት አደጋ ከመጠበቁም በላይ የእግዚአብሔርን ክብር ዝቅ እንዳናደርግ ይረዳናል፡፡ ፈርሃ እግዚአብሔር ወደ እግዚአብሔር እና ወደ እውተኛው አምላክ የሚያደርሰን ጐዳና ነው፡፡
  3. ያልተገባ ፍርሃት፡- በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚብሔር ለብዙ ሰዎች “አትፍራ፣ አትፍሪ” በማለት ሲናገር እንሰማዋለን፡፡ ምንም ዓይነት ፍርሃት ይሆን እምነት የሚያዳክመውን፣ ንፁህ ራእይ እንዳይኖረን የሚጋርደን፣ ተስፋችንን የሚያጨልመውን፣ ተጠራጣሪ፣ በቃላችን እንዳንቆም የሚያደርገንን ዓይነት ፍርሃት ነው፡፡ በዛሬው ወንጌል የምናየው እውነት ይህንኑ ነው፡፡ ሐዋርያት የነበራቸው ውጣ ውረድ ወይም ማዕበል እንዲጠራጠሩ አደረጋቸው፡፡ ስለዚህ ጌታቸውን እንኳን መለየት እስኪያቅታቸው አይናቸውን ጋረዳቸው፡፡ ነገር ግን ጌታቸውና መምህራቸው ከእነርሱ ጋር መሆኑን በተረዱ ግዜ የጌታን ኃይል አዩ፣ ተደነቁ፣ መለኮታዊ ኃይሉን ተረዱ፡፡ እያንዳንዳችን በሚገጥሙን ማዕበሎች ጌታ ትቶኛል የምንልባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ናቸው፡፡ ስለዚህ ውስጣችንን እንመልከት፣ ምናልባትም እሱ ሳይሆን እኛ እርቀን እንዳይሆን!

በሦስተኛ ደረጃ በዛሬው ቅዱስ ወንጌል ውስጥ የተጠቀሰው የእየሱስ ተግባር ደግሞ ባሕሩን በተሻገሩም ጊዜ፣ ወዲያው እንደ ወረዱም፣ ሕዝቡ ኢየሱስን አውቀውት ስለነበር፤ ወደ አካባቢውም ሁሉ በመሮጥ ሕመምተኞችን በአልጋ ላይ እየተሸከሙ እርሱ ወደ ሚገኝበት ስፍራ ሁሉ ያመጡ እንደ ነበረ፣ እነርሱም በየደረሰበት መንደር፣ ከተማና ገጠር ሕመምተኞችን በየአደባባዩ እያስቀመጡ የልብሱን ጫፍ እንኳ ለመንካት ይለምኑት ነበር፤ የነኩትም ሁሉ ይድኑ ነበር የሚለው ነው።

ኢየሱስ ወዲያውኑ ከጀልባው እንደ ወረደ ሕዝቡ ወዲያውኑ አውቁት ይለናል። ማርቆስ በዛሬው ወንጌሉ ከተለያዩ አከባቢዎች የተውጣጡ ብዙ ሕዝቦች ኢየሱስን ፍለጋ እንደ መጡ ይነግረናል። ታዲያ ይህን ያህል ብዙ ሕዝብ ኢየሱስን እንዲከተል ያነሳሳው ጉዳይ ምን ይሆን? ብለን መጠየቅ ተገቢ ይመስለኛል።

በዛሬው ቅዱስ ወንጌል እንደ ተጠቀሰው ይህ ሰፊ የሆነ ሕዝብ ኢየሱስን ፍለጋ የወጣበት ምክንያት ኢየሱስ የሚባለውን የእግዚኣብሔር ልጅ ለማየት ካደረባቸው ጉጉት የተነሳ ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ከሕመማቸውና ከተለዩዩ ደዌዎቻችው ለመፈወስ ስለፈለጉ ጭምር ነው።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ

ታዲያ ዛሬ እኔና እናንተ እየሱስን የምንፈልገው ለምንድነው? ከሕመማችን፣ ከጭንቀታችን፣ ከሽክማችን ወዘተ. . . እንዲያድነን ስለምንፈልግ ነው? ብለን እራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል። ዛሬ የምንኖርበት ዓለማችን በብዙ ነገሮች ተወጥረን እንገኛለን። ታዲያ “አይዙዋችሁ አትፍሩ እኔ ነኝ” የሚለውን እየሱስ፣ በሕይወታችን ውስጥ በእየለቱ የሚነሳውን ማእበል ለማጥፋት ብቃት ያለውን እርሱን፣ በፍርሃት በምንዋጥበት እና የዚህ ዓለም ነገሮች እንደ ማእበል ሆነው ሕይወታችንን በሚያናውጡበት ሰዓት ይህንን የሕይወት ማዕበል “ጽጥ በል” ብሎ ሊያረጋጋን ብቃት ያለውን እየሱስን፣ የሕይወታችን ዋስትና ይሆን ዘንድ እንፈልገዋለን ወይ? መልሱን ለእያንዳዳችሁ እተዋለሁኝ።

እየሱስ የዚህ ምድር ተልዕኮውን በይፋ በጀመረበት ወቅት አገልግሎቱን በስፋት የጀመረው በየመንደሩ እይዞረ በማስተማር፣ በማጽናናት፣ የሞተን በማስነሳት፣ የታመመን በመፈወስ መሆኑን የማርቆስ ወንጌል ያስተምረናል።

ለምሳሌም ጊዜው ደርሶአል፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለች፤ ንስሓ ግቡ፤ በወንጌልም እመኑ” እያለ ከሰበከበት ከገሊላ አንስቶ፣ በቅፍርናሆም  በሰንበት ቀን ወደ ምኵራብ ገብቶ ማስተማር እንደ ጀመረ፣ ወደ በረሃ መሰደዱንና በዚያም ሕዝቡ ሊፈልገው መምጣቱን፣ በባሕር ዳር ቆጭ ብሎ ሕዝቡን ማስተማሩን፣ ከፍተኛ ወደ ሆነ ስፍራ በውጣት በዚያም ሕዝቡን የተራራው ላይ ስብከት ተብሎ ይሚታወቀውን መስበኩን፣ በእየደባባዩ እና በየከተማው እየተዘዋወረ ሕሙማንን መፈወሱን፣ የመሳሰሉትን ነገሮች እየሱስ በመፈጸሙ የተነሳ ከሕዝቡ ዘንድ አድናቆት ተችሮት ነበር። በእነዚህ እና እነዚህን በመሳሰሉት ምክንያቶች ነው እንግዲህ ሕዝቡ ኢየሱስን ለመፈለግ የሚወጣው።

እየሱስ በሕዝቡ የተፈለገበት ዋንኛው ምክንያት እርሱ በሽተኞቻችውን ስለፈወሰ፣ ስላዳቸው፣ ስለአበላቸው ስለአጠጣቸው ብቻ ሳይሆን ይፈልጉት የነበሩት ነገር ግን ከእነዚህ ሥጋዊ ፍልጎቶች ባሻገር በማርቆስ ወንጌል 6:34 ላይ እንደ ተጠቀሰው “ሕዝቡ እረኛ እንደ ሌላቸው በጎች” ተጥለው የነበሩ በመሆናቸው የተነሳ ጭምር ነው። ኢየሱስ ይህንን ታሪክ በመቀየር በየሰፈሮቻቸው፣ በየቄያቸው በየከተሞቻቸው ሳይቀር እየተዘዋወረ ያስተምር ስለነበር ይህ ትሕትናው እና ትጋቱ የሕዝቡን ልብ ቆርቁሮ አነሳስቶም ነበር። የስበከውን በሕይወቱ አሳይቱዋል፣ በሕይወቱ ተጨባጭ በሆነ መልክ የኖረውን ኑሮ በቃላት ስበኮታል። ከዚህም የምንረዳው ማንኛችንም ብንሆን ሰዎችን ወደ እኛ ለመሳብ ከፈለግን፣ የክርስቶስን ቃል በመጽናት መስብክ ከፈለግን፣ ስብከታችን ውጤታማ እና ፍሬያማ መሆን የሚችለው ቃላችን ከተግባራችን፣ ተግባራችን ደግሞ ከቃላችን ጋር የተገጣጠመ ሲሆን ብቻ እንደ ሆነ ከእየሱስ ሕይወት መማር እንችላለን። ስለዚህም በዛሬው እለተ ሰንበት እየሱስ ልባችንን ከማንኛውም ፍርሃት ያላቅቅልን ዘንድ፣ በኑሮዋችን እርሱን በመምሰል በመኖር ለሌሎች በረከት የምኖንበትን ጸጋ ይሰጠን ዘንድ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማሪያም አማላጅነት ልንልምነው ይገባል። የሰማነውን በልቦናችን ያሳድርልን። አሜን!

 


ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ካ. ብርሃነየሱስ የ2009 ዓ.ም. የፍልሰታን ጾም በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት

$
0
0

የጾመ ፍልሰታ መልዕክ

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ የ2009 ዓ. ም. የጾመ ፍልሰታን በማስመልከት ለመላው ካቶሊካውያንና በጐ ፈቃድ ላላቸው ሁሉ ያስተላለፉት መልዕክት

ከሁሉ አስቀድሜ ለመላው ካቶሊካውያን ምዕመናን እንኳን ለ2009 ዓ. ም. ጾመ ፍልሰታ      በሰላም አደረሳችሁ በማለት ከነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ እስከ 15 ቀን ድረስ ምዕመናን የእመቤታችንን በረከት ለማግኘት በጾም፣ በጸሎት፣ በምህላና፣ በሱባኤ በማሳለፍ የአምላክ አንድያ ልጅ እናትና የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ለሆነችው እመቤታችን ማርያም ምሥጋና ያቀርቡላታል፡፡

ዘመነ ፍልሰታን እናቶቻችንና አባቶቻችን በእመቤታችን በመተማመን በታላቅ መንፈሳዊነት ይጾሙት እንደበረ አሁንም ወጣቶችና ታዳጊዎችም ከዓለማዊ ነገሮች በመራቅ በበለጠ መንፈሳዊነት በጾምና በጸሎት ያሳልፉታል ወንጌላዊው ዮሐንስ ማርያምን በቤቱ እንደተቀበላት ሁሉ እኛም እመቤታችንን በልባችን ውስጥ ልንቀበላት ይገባል (ዮሐ 19፡27)፡፡

የደኅንነታችንን ሥራ በመፈጸም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ አባቱ ከተመለሰ በኋላ የሁላችን ተወካይ የሆነችው ብፅዕት ድንግል ማርያም ልጇን ተከትላ በነፍስና በሥጋዋ ወደ ሰማይ ወጥታለች፣ በቅደስት ሥላሴ ፊት ደግሞ ባልዳረባ እንድትሆን ተመርጣለች ጌታችንም የእረፍት ቦታ ሆኗታል፡፡ "ይህቺ ለዘለዓለም ማረፊያ ናት" (መዝ 132፡14)፡፡

የተወደዳችሁ ምዕመናን በዚህ የጾመ ፍልሰታ ጊዜ ሁላችሁም ከፍሬ አልባ ነገር ተጠብቃችሁ ህሊናችሁን በመመርመር በመንፈሣዊነት ለመበርታትና ለመጠንከር በፍፁም ደስታ መንፈሣዊውን ጾም በመጾም ከዚህም ጐን ለጐን ችግረኞችን በመርዳት፣ በማብላትና በማልበስ የተለያዩ የበጐ ሥራ አገልግሎቶችን በመፈጸም የቅድስናን ፍሬ የምታፈሩበት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡

ወላዲት አምላክ ሁሌም ትወደስ

በእመቤታችን ጾም አማካይነት እግዚአብሔር አምላካችን እኛንና አገራችንን ይባርክ

… + ካርዲናል ብርሃነየሱስ

ሊቀ ጳጳሳት ዘካቶሊካዊያን

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዚዳንት

የምሥራቅ አፍሪካ ጳጳሳት ጉባኤዎች ኀብረት ሊቀመንበር

በዚህ የአካል እና የመንፈስ እረፍት በምናደርግበት የበጋ ወቅት ይህንን እድል ያላገኙ ሰዎችን ማሰብ ይገባል።

$
0
0

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በትላንትናው እለት ማለትም በሐምሌ 30/2009 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡት ምዕመናን፣ ነጋዲያን እና የሀገር ጎብኚዎች በእለቱ በላቲን ስርዓተ አምልኮ አቆጣጠር ደንብ መሰረት ኢየሱስ፣ ጴጥሮስንና ያዕቆብን እንዲሁም ዮሐንስን ወደ ታቦር ተራራ ብቻቸውን ይዞአቸው በወጣበት ወቅት የኢየሱስ መልክ በቅጽበት የተቀየረበት እለት በተከብረበት እለት ባደረጉት አስተንትኖ እንደ ገለጹት በዚህ የአካል እና የመንፈስ እረፍት በምናደርግበት የበጋ ወቅት (በአሁኑ ወቅት በመላው አውሮፓ በጋና ጸሐያማ በመሆኑ የተነሳ ሰዎች ከቤተሰቦቻችው ጋር የሚገኛኑበት የእረፍት ወቅት ነው) ይህንን እድል ያላገኙ በብቸኝነት የሚኖሩ፣ ጠያቂ የሌላቸው፣ የታመሙ፣ ድኸ የሆኑ በጦርነት እና በብጥብጥ ብሎም በፍትህ መጓደል ምክንያት እየተሰቃዩ የሚገኙ በዓለም ዙሪያ የኒገኙትን ወንድም እና እህቶቻችንን ማሰብ ይገባናል ብለዋል።

“የእየሱስ መልክ የተቀየረበት አጋጣሚ ለእኛ የተስፋ መልእክት ያስተላልፍልናል፣ ወንድሞቻችንን ማገልግል እንችል ዘንድ በቅድሚያ እየሱስን እንድንገኛ ጥሪ ያቀርብልናል” በማለት አስተንትኖዋቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው “በዛሬው እለት ቅዱስ ወንጌል ውስጥ የተጠቀሰው በታቦር ተራራ የተፈጠረው በዓይነቱ ልዩ የሆነ ክስተት እውነተኛነቱ በሐዋሪያው ጴጥሮስ፣ በያዕቆብ እና በዩሐንስ የተመሰከረ ትይን እንደ ሆነም ቅዱስነታቸው ገልጸዋል።

ይህ በሦስቱ ደቀ መዝሙር የተመሰከረው ክስተት “ወደ ሰማያው ቤታችን የምናደርገው ጉዞ የተሳካወይም ደግሞ ውጤታማ ይሆን ዘንድ  ከዓለማዊ ነገሮች መላቀቅ እንደ ሚያስፈልግ እንድናስብ ያደርገናል” ያሉት ቅዱስነታቸው የእግዛኢብሄርን ቃል በተሟላ መልኩ ለመቀበል ያስችልነ ዘንድ ጥልቅ የሆነ ጸሎት የምናደርገብት ውቅቶችን እንድንፈልግ ያደርገናል ብለዋል።

“በወንጌል ቃላት ላይ አስተንትኖ የምናደርግበት፣ መጽሐፍ ቅዱስነት የምናነብበት፣ መልካም የሆኑ ነገሮችን የምንመኝበት፣ የምንደምቅበት እና ደስታ የምናገኝበትን ሰላም የሰፈነበት ሁኔታ ፈልገን እንድናገኝ ጥሪ ያደርግልናል” በማለት አስተንትኖዋቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው ይህ አካላዊ እና የመንፈስ እረፍት የምናደርገበት የበጋው የእረፍት ወቅት “እየሱስን ለማግኘት ጥብቅ ፍለጋ የምናደርግበት ወቅት” ሊሆን ይገባል ብለዋል።

“በዚህ አካልዊ እና የመንፈስ እረፍት በምናደርገበት በአሁኑ የበጋ ወቅት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው የሚያርፉበት፣ ብዙ ቤተሰቦች እረፍት በሚያደርጉበት በአሁኑ ወቅት እለታዊ ከሆኑ ጭንቅቶቻችን መላቀቅ ይኖርብናል” ያሉት ቅዱስነታቸው በእለታዊ ጭንቀቶች ምክንያት የደከመውን አካላችንንና እና መንፈሳችንን ለማደስ መንፈሳዊ ሕይወታችንን በጥልቅ መመርመር ይኖርብናል ብለዋል።

ይህንን የእረፍት ጊዜያችን የተረጋጋ ይሆን ዘንድ፣ ይህንን የእረፍት ጊዜ በእድሜ ምክንያት በተፈለገው መልኩ መጠቀም ያልቻሉትን አረጋዊያን፣ በጤና እክል ወይም ደግሞ በሥራ ምክንያት፣ በገንዘብ እጥረትና በመሳሰሉት ምክንያቶች በተገቢው ሁኔታ የእረፍት ጊዜ ማድረግ ባለመቻለቸው የተነሳ ያዘኑና የብቸኝነት ስሜት የሚሰማቸውን ሰዎች ታጽናና ዘንድ ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም በአደራ ልንሰጥ ይገባል ካሉ ቡኃላ “የእግዛኢኣብሔር መልአክ ማሪያምን አበሰራት እርሷም በመንፈስ ቅዱስ ጸነሰች” የሚለውን ጸሎት ከምእመናን ጋር በመቀባበል ደግመውና ቡራከን ሰጥተው የእለቱን አስተንትኖዋቸውን አጠናቀዋል።

 

 

 

ቅዱስ ኣባታችን ር.ሊ.ጳ.፥ ከድኾች ጋር ስንገናኝ ከእኛ ጋር ሊገናኝ ከሚመጣው ክርስቶስ ጋር እንገናኛለን

$
0
0

ሌላው ከእኔ የተለየውን በአክብሮት ማስተናገድና መቀበል በእርሱ ውስጥ ያለው በተለይ ድግሞ ድኻና ጎስቋላ በቀላሉ ለአደጋ የተጋለጠ ከሆነ በእርሱ ውስጥ እኔን ለማግኘት የሚመጣው ክርስቶስን ነው የማስተናግደው የሚል በድኻውና በጎስቋላው በተጨቆነው ውስጥ የሚገለጠውን ክርስቶስ መቀበል ለአንድ ክርስቲያን ትልቅ ክብር መሆኑ የሚያብራራ ሃሳብ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ትዊተር በተሰየመው ማኅበራዊ መረብት ባለው @Pontifex በተሰየመው አድራሻቸው አማካኝነት ባስተላለፉት መልእክት እንዳሰመሩበት የቫቲካን ረዲዮ ልእክት ጋዜጠኛ ኤማኑኤላ ካምፓኒለ ገለጡ።

ቅዱስነታቸው በዚህ የትዊተር መልእክታቸው አማካኝነት ለሚሰቃየው ለድኻው ለተናቀውና በተለያየ ዘርፈ ብዙ ችግር አማካኝነት ተነጥሎ ለሚኖረው ያላቸው ጥልቅ ቅርበት ይመሰክራሉ። ወደ ጥጋ ጥግ የከተሞቻችንና የህልውና ክልል የማይል ክርስትና እምነት ሊሆን አይችል ወይንም ክርስቶስን የሚከተል ነው ብሎ ለመናገር እንደማይቻልም በማመላከት ማኅበረ ክርስቲያንና ቤተ ክርስቲያንን ክርስቶስ በመምሰል ሂደት እንዲያድጉ ይመክራሉ።

ባለ እንጀራና ጎረቤት የሚለው ብዙውን ጊዜ ኢየሱስ ስለ ሚገልጠው ቃል፡ እንደ ገዛ እራስህ አፍቅር የሚለው ምዕዳኑን እንዲስተዋል የሚያመላክት ነው፡ ይኽ ክርስቶሳዊ ጥሪ ቅዱስ አባታችን የሐዋርያዊ ግብረ ኖልዎ ማእከል እንዲሆንና በሃሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባር መተርጎም የሚገባው ክርስቶስ ለእኛ ያለው ቅርበት ማረጋገጫ መሆኑ ያስተምራሉ። ካለ ማቋረጥም ዘወትር አደራ የሚሉት ሥልጣናዊ ምዕዳንም መሆኑ ካምፓኒለ ያስታውሳሉ።

ሌላውን ምንም የሌለውን ነጥሎ እንደ ቆሻሻ ተመልክት የሚለው ሰው በመሆኑ ሳይሆን በሚኖረው ሃብት መከበር አለበት የሚለውን ባህል ሌላውን በመቀበል በቃልና በተግባር መዋጋት እንዳለብን፡ ሌላው ክእኔ ጋር ለመገናኘት የሚመጣ ክርስቶስ ነው ይኸንን በስብከታቸው በሥልጣናዊ ትምህርታቸው በሚፍጽሟቸው ዓለም አቀፍም ይሁን ብሔራው ሐዋርያዊ ጉብኝቶች ካለ መታከት የሚያሰምሩበት ክርስቶሳዊ ሃሳብ ነው። እ.ኤ.አ. ህዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም. አገረ ቫቲካን በሚገኘው በጳውሎስ ስድተኛ የጉባኤ አዳራሽ፥ ከሰባት ሺሕ በላይ የሚገመቱ ከውጭና ከውስጥ የመጡት ምእመናን የኢጣሊያ ህሙናንና ጉዳተኞች ወደ ቅዱሳት ሥፍራዎች መንፈሳዊ ንግደት የሚሸኝ ማኅበር 110ኛ ዓመተ ምሥረታ ምክንያት ተቀብለው፥ ግብረ ሠናይ ወንጌላዊ ተግባር ነው በማለት በተለያየ የግብረ ሠናይ አገልግሎት የተሰማሩት የበጎ ፈቃድ አባላት በዓለም በሚታየው ስቃይና መከራ በሚሰቃየው ሰው ሁሉ ፊት ያንን በኢየሱስ የተገለጠው እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ፍቅር መስካሪያን ሁኑ፡ ድኻው የሚሰቃየው የክርስቶስ አካል ነው” ብለው እንደነበር የቫቲካን ረዲዮ ልእክት ጋዜጠኛ ካምፓኒለ ባጠናቀሩት ዘገባ  በማስታወስ ጠቅሰዉታል።

እስያ አቀፍ የካቶሊክ ወጣቶች ቀን

$
0
0

ከሃያ አንድ የእስያ አገሮች የተወጣጡ ካቶሊክ ወጣቶች ያሳተፈው በኢንዶነዢያ ርእሰ ከተማ ጃካርታ የተካሄደው እስያ አቀፍ ሰባተኛው የካቶሊክ ወጣቶች ቀን እ.ኤ.አ. ሐምሌ 30 ቀን ተጀሮ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 6 ቀን 2017 ዓ.ም.  መጠናቀቁ ኤሺያን ኔውስ የዜና አገልግሎት አስታወቀ።

ይኽ ጃካርታ በሚገኘው ወታደራዊ አየር ማረፊያ አደባባይ የአገሪቱ ምክትል ርእሰ ብሔር ጁኡፍ ካላ በተገኙበት ባረገው መሥዋዕተ ቅዳሴ የተጠናቀቀው የእስያ አገሮች ካቶሊክ ወጣቶች ቀን ምክንያት ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ የቅድስት መንበር ዋና ጸሓፊ ብፁዕ ካርዲናል ፒየትሮ ፓሮሊን ፊርማ የተኖርበት ባስተላለፉት መልእክት፥ የእስያ ካቶሊክ ወጣቶች በእምነትና በጽናት መልስ የሚሰጡበት ከጌታ የሚቀርብላቸውን ጥሪ በጥልቅ እንዲያዳምጡ አደራ በማለት ወጣቶች የማርያም ለጋስነት እነሆኝ ባይነት እራስነትን በሙላት ለጌታ እቅድ የማቅረቡን አርአያ አስተንፍሶ በማድረግ ሐዋርያትና ልኡካነ ወንጌል እንዲሆኑ ለማርያም አፍቃሪው እናትነት ገዛ እራሳቸውን እንዲያወክፉና በእርሷ አማላጅነትም እንዲጸልዩ ማሳሰባቸው ኤሺያን ኔውስ የዜና አገልግሎ አስታወቀ፡

ይኽ በኅብረ ባህል በሆነችው እስያ ወንጌል መኖር በሚል ቃል ሥር ተመርቶ የተካሄደው የእስያ ካቶሊክ ወጣቶች ቀን በማስመልከት ከቫቲካን ረዲዮ ጋር ቃለ ምልልስ ያካሄዱት የፊሊፒንስ ርእሰ ከተማ ሊቀ ጳጳስ የተለያዩ የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የተራድኦ ማኅበራትን የሚያቅፈው በካሪታስ ኢንተርናዚዮናሊስ ለሚጠራው ማኅበር ሊቀ መንበር ብፁዕ ካርዲናል ልዊስ አንቶኒዮ ታግለ፥ በእስያ ካቶሊክ ወጣቶች ቀን ሲገኙ ለሦስተኛ ጊዚያቸው እንደሆነ በማስታውስ፡ በዚህ ኅብረ ባህልና ኅብረ ሃይማኖት በሚኖርበት ክፍለ ዓለም የሚኖሩት ካቶሊክ ወጣቶች እርስ በእርስ በመገናኘት ባህል በመኖርና ኅብረአዊነት የሚያቀራርብ ለመተዋወቅ የሚገፋፋ ክብር መሆኑ በማስተዋል ልዩነት የሰላም መሣሪያ እንዲያደርጉ በስፋት ጥሪ የቀረበበትና በዚህ ጉዞም የሕይወት ምስክርነት የቀረበበት ውይይት መከባበርና መቀራረብ ለአንድ ኅብረተሰብ ለሰላማዊ ማኅበራዊ ኑሮ መሠረት ነው፡ ልዩነት የመገነጣጠል የመከፋፈል የማግለያ መሣሪያ ሳይሆን የአንድ ኅብረተሰብ የሥልጣኔዊ ሃብት መሆኑ ይኽ የተካሄደው የእስያ ካቶሊክ ወጣቶች ቀን ተጨባጭ ምስክር ነው ብሏል።

ኢንዶነዢያ ለሁሉም የእስያ አግሮች አቢይ ትርጉም ያላት አገር ነች። ምክንያቱም የኢንዶነዢያ አገር አበው አገሪቱ የኅብረ ባህል የኅብረ ሃይማኖት አገር እንድትሆንና የሕሊና ነጻነት ሁሉም የሚከተለውን ሃይማኖት በመኖር ከጥልቅ ሃይማኖታዊ ክብር በመደርደር አብሮ ይኸንን ያላትን ኅብረአዊነት በማክበር እንድትኖር ያደረጉ በመሆናቸው፡ ይኽ እሴት ለሁሉም እስያ አገሮች አብነት ነው፡ በመሆኑም ይላሉ ብፁዕነታቸው፥ በጃካርታ የተካሄደው የእስያ ካቶሊክ ወጣቶች ቀን የተዋጣለት የኅብረ ባህልና ኅብረ ሃይማኖት ለመቀራረብ መሠረት መሆኑ አስረግጦ መስክሯል።

ለማቀራረብ የሚያስችል እድል መፍጠር እንጂ የሚለያይ ግንብ ሰላም የሚያረጋግጥ ሳይሆን እርስ በእርስ ተፈራርቶ ለመኖርና ለከፋ ማኅበራዊ ሰብአዊ ችግር የሚያጋልጥ መሆኑ ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች። ልዩነት ለማቀራረብ የሚያነቃቃ አቢይ ውስጣዊ ግፊትና እድል እንደሆነ የሚያተኵር ኅብረተሰብ ሰላማዊ ማኅበራዊ ኑሮ ይኖረዋል። ለዚህም ነው ልዩነት የሚያገናኝ ሃብት እንጂ ለያይ አጥር አስገንቢ ምክንያት ሊሆን አይችልም የሚባለው። ባህላዊም ይሁን ሃይማኖታዊ ልዩነት ለመተዋወቅ የሚገፋፋ ጉጉት እንጂ ለመገነጣጠል በጠላትነት መንፈስ ለመተያየት የሚገፋፋ ምክንያት ሊሆን እንደሚያይገባው ያሳሰቡት ብፁዕ ካርዲናል ታግለ አያይዘው፥ ድኾችን የማይረሳ ወደ የክልሎችና የህልውና ጥጋ ጥግ ክልል የሚል ኅብረተሰብ የመገናኘት ባህል ድኻውንና የተነጠለውን በተለያየ ምክንያት ተነጥሎ እንዲኖር የተግደደውን ማቅረብ የሚለው በተደጋጋሚ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ የሚያስተላፉት ሥልጣናዊ ትምህርት ካልታከለበት በእውነቱ ሰላማዊ የአብሮ መኖር ባህል እውን ማድረግ አይቻልም።

በዓለማችን የሚታየው ህልውናዊ ባህላዊ ኤኮኖሚያዊ ተገሎነት እንዲቀረፍ ተገሎ ወደ ሚኖረው ማቅናትና ለተገለለው ቅርብ መሆን ያስፈልጋል። በተለያየ መልኩ የሚታየው ሕዳጣንነት ለቤተ ክርስቲያንና ለምእመናንዋ ለአስፍሆተ ወንጌል ምክንያት መሆን አለበት። አብላጫው ሃይማኖትም ይሁን አብላጫው ባህል ለሕድጣኑ አምባገነን መሆን የለበትም እንዳውም ሕዳጣኑ ባህሉንና ሃማኖቱን እንዲኖር በማድረግ ኅብረአዊነት ሃብት መሆኑ እንዲመሰክር የሚያነቃቃ መሆን ይገባዋል። ይህ በሃይማኖት ብቻ ሳይሆን በሁሉም መስክ ሊኖር የሚገባው ክብር ነው፡ ይኽ እሴት በኢንዶነዢያ የተካሄደው ሰባተኛው የእስያ ካቶሊክ ወጣቶች ቀን በትክክል መስክሮታል በማለት ያካሄዱት ቃለ ምልልስ አጠቃሏል።     

ሥነ ምህዳራዊ ቲዮሎጊያ፥ ተፈጥሮን ለመንከባከብና በሚገባ መንገድ ለመጠቀም

$
0
0

የሕይወት ባህል መሠረት ያደረገ የእግዚአብሔር ዱካ በፍጥረት ሁሉ ህልውናውን በመለየት ተግባራችንን ተፈጥሮ ለመጠቀም የምንከተለው ሥልት ሁሉ በጥልቀት ለመመርመር የሚያግዝ በሥነ ምህዳራዊ ቲዮሎጊያ ዙሪያ ጥልቅ አስተንትኖ ማድረግ ያለው አስፈላጊነት በሁሉም ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በምትገኝበት ክልል እየትገለጠ መሆኑ ኮምቦናዊ ካህን አባ ዳሪዮ ቦሲ በስልክ ከቫቲካን ረዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ ገልጠው፥ የአማዞንን ክልል ለመከላከል ሰው በተፈጥሮ ላይ የሚፈጽመው አመጽ በዚህ የአማዞን ክልል አበይት ኢንዳስትሪዎች ለመገንባት በሚል የተፈጥሮና የፍጥረት ጤንነት ግድ የማይሰጥ አርቆ የማይመለከት ትርፍ ማከበት ብቻ የሚል እቅድ ላይ የጸናው የሚከተሉት የኤኮኖሚ ሂደት የሚያስከትለው ሰብአዊ ማኅበራዊና ምኅዳራዊ ችግር በጥልቀት የሚያብራራ የሥነ ምኅዳር ቲዮሎጊያ ዙሪያ የሚመክር ቀዳሚ ዓውደ ጥናት እ.ኤ.አ. ነሐሴ 16ና 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በብራዚል እንዲካሄድ በእቅድ መያዙ ባካሄዱት ቃለ ምልልስ አስታውቋል።

የመላ አማዞን ቤተ ክርስቲያናዊ መረብትና የቤተ ክርስቲያንና በማዕድን ሃብት የታደሉ ክልሎች መረብት አማካኝነት ይኽ በብራዚል ሊካሄድ የተወሰነው በዓይነቱ ቀዳሚ የሆነው የሥነ ምኅዳራዊ ቲዮሎጊያ ዓውደ ጥናት ቤተ ክርስቲያን ከአገሬው ሕዝብና እንዲሁም እናት ተፈጥሮን በመንከባከብ ረገድ አብራ በመጓዝ በዚህ በአሁኑ ሰዓት የዓለም ኤኮኖሚ ቅጥ የለሽ እየሆነ በምኅዳርና በሰው ልጅ ባጠቃላይ በፍጥረት ላይ እያስከተለው ያለው ችግር ለይቶ ተፈጥሮና ሕዝብን ለመከላከል ምን መደረግ አለበት ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠትና የሥነ ምኅዳር ጥሪ ለይቶ በማብራራት ሰው የተፈጥሮ ባላባት ሳይሆን አቃቢ ተከባካቢ መሆኑ እንዲገነዘብ ለማድረግ ያለመ ዓውደ ጥናት መሆኑ አባ ቦሲ ገልጠዋ።

ዓውደ ጥናቱ ለየት ባለ መልኩም ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ይሴባሕ በሚል ርእስ ሥር በተፈጥሮና በፍጥረት ዙሪያ ሥልጣናዊ ትምህርት የሰጡበት አዋዲ መልእክት መሠረት በማድረግና ይኸንን ዓዋዲ መልእክት በጥልቀት የሚያስተነትን የክልሉ ሁኔታ የሚያገናዝብ ነው ካሉ በኋላ ከአገርየው ሕዝብ ከተለያዩ ማኅበራዊና ምኅዳራውያን እንቅስቃሴዎች ጋር በመተባበር የሚመክርና ስለ ሥነ ምኅዳራዊ ቲዮሎጊያ ጥልቅ አስተንትኖ የሚደረግበት ዓውደ ጉባኤ ይሆናል ሲሉ ያካሂዱት ቃለ ምልልስ አጠቃለዋል።

"መለኮታዊ ምሕረት የክርስቲያን ተስፋ መሰረት ነው" ር.ሊ.ጳ .ፍራንቸስኮ

$
0
0

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራቸስኮ ዘወትር ረዕቡ እለት በቫቲካን ለሚሰበሰቡ ምዕመናን፣ ነጋዲያን እና የሀገር ጎብኚዎች በተለያዩ አርእስቶች ዙሪያ የትምህረተ ክርስቶስ አስተምህሮ እንደ ሚያደርጉ ይታወቃል። የዚሁ መርሀ ግብር አንዱ አካል በሆነው በሐምሌ 3/2009 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው በጳውሎስ 6ኛ አዳራሽ ያደረጉት የትምህረተ ክርስቶስ አስተምህሮ ትኩረቱን ያደረገው በሉቃስ ወንጌል 7:36-50 ላይ የነበረ  ሲሆን በዚሁ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ውስጥ አንዲት ሴት የኢየሱስን እግር ሽቶ መቀባቷን በሚያመለክተው የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ዙሪያ ላይ ያጠነጠነ እንደ ነበረ ለመረዳት ተችሉዋል።

የዚህን አስተምህሮ ሙሉ ይዘት ከዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!

 

በእለቱ የተነበበው ቅዱስ ወንጌል ሉቃስ 7:36-50

“ከዚህ በኋላ ከፈሪሳውያን አንዱ ምግብ አብሮት እንዲበላ ኢየሱስን ጋበዘው፤ እርሱም ወደ ፈሪሳዊው ቤት ሄዶ በማእድ ተቀመጠ። በዚያ ከተማ የምትኖር አንዲት ኀጢአተኛ ሴት፣ ኢየሱስ በፈሪሳዊው ቤት በማእድ መቀመጡን በሰማች ጊዜ አንድ የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ሽቶ ይዛ መጣች፤ ከበስተ ኋላው እግሩ አጠገብ ቆማ እያለቀሰች እግሩን በእንባዋ ታርስ፣ በራሷም ጠጒር ታብሰው ጀመር፤ እግሩንም እየሳመች ሽቱውን ቀባችው።

የጋበዘውም ፈሪሳዊ ይህን ባየ ጊዜ፣ይህ ሰው ነቢይ ቢሆን ኖሮ፣ የነካችው ሴት ማን እንደሆነች፣ ደግሞም ምን ዐይነት ሰው እንደሆነች ባወቀ ነበር፤ ኀጢአተኛ ናትናብሎ በልቡ አሰበ። ኢየሱስም፣ “ስምዖን ሆይ፤ የምነግርህ ነገር አለኝ” አለው። እርሱም፣መምህር ሆይ፤ ንገረኝአለው።

ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “ከአንድ አበዳሪ ገንዘብ የተበደሩ ሁለት ሰዎች ነበሩ፤ አንደኛው አምስት መቶ ዲናር፣ ሁለተኛው ደግሞ አምሳ ዲናር ነበረበት። የሚከፍሉትም ቢያጡ ዕዳቸውን ለሁለቱም ተወላቸው። እንግዲህ ከሁለቱ አበዳሪውን አብልጦ የሚወደው የትኛው ነው?” ስምዖንም፣ብዙው ዕዳ የተተወለት ይመስለኛልሲል መለሰ።

ኢየሱስም፣ “ትክክል ፈርደሃል” አለው።

ወደ ሴቲቱም ዘወር ብሎ ስምዖንን እንዲህ አለው፤ “ይህቺን ሴት ታያታለህን? እኔ ወደ ቤትህ ገባሁ፤ አንተ ለእግሬ ውሃ እንኳ አላቀረብህልኝም፤ እርሷ ግን እግሬን በእንባዋ እያራሰች በጠጒሯ አበሰች። አንተ ከቶ አልሳምኸኝም፤ እርሷ ግን ከገባሁ ጀምራ እግሬን ከመሳም አላቋረጠችም። አንተ ራሴን ዘይት አልቀባህም፤ እርሷ ግን እግሬን ሽቶ ቀባች። ስለዚህ እልሃለሁ፤ እጅግ ወዳለችና ብዙው ኀጢአቷ ተሰርዮላታል፤ በትንሹ የተሰረየለት ግን የሚወደው በትንሹ ነው።

ኢየሱስም ሴቲቱን፣ “ኀጢአትሽ ተሰርዮልሻል” አላት። አብረውት በማእድ ተቀምጠው የነበሩ እንግዶችም፣ይህ ኀጢአትን እንኳ የሚያስተስረይ እርሱ ማን ነው?” ብለው በልባቸው አሰቡ። ኢየሱስም ሴቲቱን፣ “እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ” አላት” (ሉቃስ 7:36-50)

 

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በቫቲካን በሚገኘው የጳውሎስ 6ኛ አዳራሽ ለተሰበሰቡ ምዕመናን ያደረጉትን የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ሙሉ ይዘቱን እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል እንድትከታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደ ምን አረፈዳችሁ

ከፈሪሳውያን አንዱ ምግብ አብሮት እንዲበላ ኢየሱስን በቤቱ በጋበዘው ወቅት አብረውት በማእድ ተቀምጠው የነበሩ ፈሪሳዊው  ስምዖን እንግዶችይህ ኃጢአትን እንኳ የሚያስተስረይ እርሱ ማን ነው?” (ሉቃ. 7:49) ብለው ተናግረው እንደ ነበር ከዛሬው ቅዱስ ወንጌል ሰምተናል።  ኢየሱስ ይህንን ተግባር በፈጸበት ወቅት በዚያ የነበሩ ሰዎች የአሉባልታ ወሬ ሰለባ ሆኑዋል። በዚያ ከተማ የምትኖር አንዲት በሁሉም ዘንድ የምትታወቅ ኃጢአተኛ ሴት፣ ኢየሱስ በፈሪሳዊው ቤት በማእድ መቀመጡን በሰማች ጊዜ አንድ የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ሽቶ ይዛ መጣች፤ እግሩንም እየሳመች ሽቱውን ቀባችው። ይህንን የተመለክቱት በዚያ የነበሩ ሰዎችይህ ሰው ነቢይ ቢሆን ኖሮ፣ የነካችው ሴት ማን እንደሆነች፣ ደግሞም ምን ዐይነት ሰው እንደሆነች ባወቀ ነበር፤ ኀጢአተኛ ናትናበማለት  በዚያ ግብዣ ላይ የነበሩ ሰዎች ማጉረምረም ጀመሩ። በእርግጥ በዚያን ወቅት ቅዱስ በሆነ ሰው እና ኃጢአተኛ በሆነ ሰው መካከል፣ ንጹዕ በሚባል ሰው እና ባልነጻ ሰው መካከል፣ ያለው ልዩነት ግልጽ በሆነ መልኩ ሊቀመጥ የገባዋል የሚል አስተሳሰብ ነበረ።

ነገር ግን ኢየሱስ ያሳየው ከእዚህ አስተሳሰብ ለየት ያለ ባሕሪ ነበረ። አገልግሎቱን በይፋ ከጀመረበት ከገሊላ አንስቶ እርሱ በለምጽ በሽታ የተጠቁ ሰዎችን፣ ክፉ መንፈስ የተጠናወታቸው ሰዎች፣ የታመሙትን እና የተገለሉ ሰዎችን ይቀርብ ነበር። የዚህ ዓይነቱ ባሕሪ ግን ወቅቱ የተለመደ ባሕሪ አልነበረም፣ እውነት ነው ኢየሱስ ለተገለሉ ሰዎችና ሰዎች ለመንካት እንኳን ለሚጸየፉቸውን ሰዎች የሚያሳየው ርኅራኄ በዚያን ዘመን የነበሩትን ሰዎች የሚረብሹ ተግባር መሆኑ እሙን ነው። አንድ ሰው በሚሰቃይበት ወቅት ኢየሱስ የዛን ሰው ስቃይ የራሱ በማድረግ ያን ሰው ይንከባከበዋል። አንድ ሰው ማንኛውም ዓይነት የቅጣት ሁኔታ በጀግንነት መቋቋም አለበት ብሎም አልሰበከም። ማንኛውንም የተቸገረ ሰው በሚገናኝበት ወቅት ኢየሱስ የሰዎችን መከራ በመካፈል የክርስቲያን መገለጫ ባሕሪ የሆነውን ምሕረቱን ያሳያቸዋል። በግርዱፉ ሲታይ የዚህ ዓይነት ሁኔታ ስያጋጥመው ኢየሱስ አንጀቱን ይበላዋል። ይህንንም ተግባሩን በቅዱስ ወንጌል ውስጥ በብዙ ቦታዎች ውስጥ እናገኘዋለን። ኢየሱስ የነበረው የልብ ዓይነት የእግዚኣብሔር ልብ  መገለጫ የነበረ ሲሆን በዚህም ምክንያት አንድ ወንድ ወይም ሴት በሚሰቃዩበት ሥፍራ የእነርሱን ፈውስ የሚመኝ፣ የእነርሱን ነጻ መውጣት የሚፈልግ፣ ምልአት ያለው ሕይወት እንዲኖሩ የሚፈልግ የሥጋ ልብ ነበር የነበረው።

ኢየሱስ እጆቹን ለኃአጢያተኞች የሚዘረጋው በዚሁ ምክንያት ነው። ዛሬም ቢሆን በእግዚኣብሔር ልብ ተሞልተው ይህም ማለት በተስፋ ተሞልተው የሚመራቸውና መንገድ የሚያሳያቸው ሰው በማጣታቸው የተነሳ በተሳሳተ ጎዳና ላይ የሚረመዱ ብዙ ሰዎች አሉ። ኢየሱስ ግን በጣም ብዙ የተባለ የተከማቼ ስህተት ያላቸውን ሰዎች ሳይቀር ከዚህ ሸክማቸው የሚያላቅቃቸው የትንሣኤ እድል ይሰጣቸዋል።

ከዚህም እግዚኣብሔር ቤተክርስቲያኑን የመሰረተበት ምክንያት መቼም ቢሆን የማይሳሳቱ ሰዎች ለመሰብሰብ ብቻ ፈልጎ እንዳልሆነ እንረዳለን። ቤተክርስቲያን ማለት ኃጢኣተኛ የሆኑ ሰዎች የእግዚኣብሔርን ምሕረት እና ይቅርታ የሚያገኙበት ሥፍራ ማለት ነው።  ጴጥሮስ ያከናውናቸው የነበረው መልካም ሥራዎቹ ልቡን በማሳበጥ ከሌሎች የበላይ እንደ ሆነ የሚሰማው ስሜት እንዲያስወግድ ያደረገውና ስለራሱ ማንነት እውነታውን የተረዳው ዶሮ በጮኸበት ወቅት ነበር።

ኃጢኣተኞች ከኃጢኣታቸው የሚነጹት በዚሁ መልኩ ነው። ኢየሱስ የተሳሳተ የሕይወት መንገድ ለነበራቸው ሰዎች ሁሉየአዲስ ሕይወት ተስፋ ይሰጣቸዋል፣ በፍቅር የተሞላ ሕይወትም ያጎናጽፋቸዋል። ቅራጭ የነበረው ማቴዎስ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ሆኑዋል። የኢየሪኮ ሀገር ሰው የነበረው ሀብታም ሙሰኛው  ዘኪዮስ፣ ለድኾች የበጎ አድርጎት ተግባር የሚፈጽም ሰው ሆኑዋል።  የሰማሪያ ሀገር ሰው የነበረችሁና ከዚህ ቀደም አምስት ባሎች የነበሩዋት ነገር ግን አሁን ከአንዱ ጋር ብቻ እየኖረች የነበረቺው ሴት “ጌታዬ፤ እንዳልጠማና ውሃ ለመቅዳት እንዳልመላለስ፣ እባክህ ይህን የሕይወት ውሃ ስጠኝ” (የሐንስ። 4:14) በማለት መንፈሳዊ ጥማቱዋን ገልጻለች።

ሁላችንም ምስኪን ኃጢኣተኞች  በመሆናችን የተነሳ ሊቀይረን የሚችል ኃይል ያለውና በእየለቱ  ተስፋ የሚሰጠን የእግዚኣብሔር ምሕረት ያስፈልገናል። ይህንን መሰረታዊ እውነተ ለተገነዘቡ ሰዎች እግዚኣብሔር በዓለም ውስት ውብ የሆነ ተልእኮን ይሰጣቸዋል፣ ይህም ማለት ለወንድሞቻችን እና ለእህቶቻችን እርሱ ለማንም የማይከለክለውን ምሕረቱን ማወጅ ነው።

 

የነሐሴ 7/2009 ዓ.ም. እለተ ሰንበት ምንባባት እና አስተንትኖ በክቡር አባ መብራቱ ኃይለጊዮርጊስ

$
0
0

የነሐሴ 7/2009 ዓ.ም. እለተ ሰንበት ምንባባት እና አስተንትኖ በክቡር አባ መብራቱ ኃይለጊዮርጊስ

  1. ቆሮ 81-13   ለጣዖት የተሠዋ ሥጋ

    ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋ ደግሞ ይህን እላለሁ፤ ሁላችንም ዕውቀት እንዳለን እናውቃለን ዕውቀት ያስታብያል፤ ፍቅር ግን ያንጻል። ዐውቃለሁ የሚል ሰው፣ ማወቅ የሚገባውን ያህል ገና አላወቀም። እግዚአብሔርን የሚወድ ሰው ግን በእግዚአብሔር ዘንድ የታወቀ ነው።

    እንግዲህ፣ ለጣዖት የተሠዋ ሥጋ ስለ መብላት እንዲህ እላለሁ፤ በዚህ ዓለም ጣዖት ከንቱ እንደሆነና ከአንዱ ከእግዚአብሔር በስተቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ እናውቃለን። መቼም ብዙ አማልክትና ብዙ ጌቶች አሉ፤ በሰማይም ሆነ በምድር አምላክ ተብለው የሚጠሩ አማልክት ቢኖሩም፤ ለእኛ ግን ሁሉም ነገር ከእርሱ የሆነ፣ እኛም ለእርሱ የሆን አንድ አምላክ አብ አለን፤ ደግሞም ሁሉም ነገር በእርሱ አማካይነት የሆነ፣ እኛም በእርሱ አማካይነት የሆን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አለን።

    ነገር ግን ይህን የሚያውቁ ሁሉም አይደሉም፤ አንዳንድ ሰዎች እስከ አሁን ድረስ ጣዖትን ማምለክ ስለ ለመዱ፣ እንዲህ ያለውን ሥጋ ሲበሉ በርግጥ ለጣዖት እንደ ተሠዋ ያስባሉ፤ ኅሊናቸውም ደካማ ስለ ሆነ ይረክሳል። ነገር ግን ምግብ ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላ የሚጐድልብን ነገር የለም፤ ብንበላም የምናተርፈው ነገር አይኖርም።

    ነገር ግን ከነጻነታችሁ የተነሣ የምታደርጉት ለደካሞች ዕንቅፋት እንዳይሆን ተጠንቀቁ። አንተ ይህን የመሰለ ዕውቀት ኖሮህ፣ ደካማ ኅሊና ያለው ሰው በቤተ ጣዖት ስትበላ ቢያይህ፣ ለጣዖት የተሠዋውን ምግብ ለመብላት አይደፋፈርምን? ስለዚህ ክርስቶስ የሞተለት ይህ ደካማ ወንድም በአንተ ዕውቀት ምክንያት ጠፋ ማለት ነው። በዚህ መንገድ ወንድሞቻችሁን በመበደልና ደካማ ኅሊናቸውን በማቍሰል፣ ክርስቶስን ትበድላላችሁ። ስለዚህ እኔ የምበላው ነገር ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ፣ ወንድሜን ላለማሰናከል ስል ከቶ ሥጋ አልበላም።

     

    ለእግዚአብሔር መኖር

    እንግዲህ ክርስቶስ በሥጋው መከራን ስለ ተቀበለ እናንተም በዚሁ ዐላማ ታጥቃችሁ ተነሡ፤ ምክንያቱም በሥጋው መከራን የሚቀበል ሰው ኀጢአትን ትቶአል። ከዚህም የተነሣ ከእንግዲህ በሚቀረው ምድራዊ ሕይወት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ምኞት አይኖርም። አሕዛብ ፈቅደው እንደሚያደርጉት በመዳራት፣ በሥጋዊ ምኞት፣ በስካር፣ በጭፈራ፣ ያለ ልክ በመጠጣት፣ በአስጸያፊ የጣዖት አምልኮ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል። ይህን በመሰለ ብኩን ሕይወት ከእነርሱ ጋር ስለማትሮጡ እንግዳ ሆኖባቸው በመደነቅ ይሰድቧችኋል። ነገር ግን በሕያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ ለተዘጋጀው መልስ ይሰጣሉ።

    1. 1 ጴጥሮስ  4:1-5

 ወንጌል 12:38-50ተአምራት ለማየት የቀረበ ጥያቄ

 

ከዚያም አንዳንድ የአይሁድ ሃይማኖት መምህራንና ፈሪሳውያን፣ “መምህር ሆይ፤ ከአንተ ታምራዊ ምልክት ማየት እንፈልጋለን” አሉት። እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክትን ይጠይቃል፤ ነገር ግን ከነቢዩ ዮናስ ምልክት በስተቀር ሌላ ምልክት አይሰጠውም። ዮናስ በዓሣ ዐንበሪ ሆድ ውስጥ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ቈየ፣ እንዲሁ የሰው ልጅ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በምድር ሆድ ውስጥ ይቈያል። የነነዌ ሰዎች በፍርድ ዕለት ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ እነርሱ በዮናስ ስብከት ንስሓ ገብተዋልና። እነሆ፤ ከዮናስ የሚበልጥ እዚህ አለ። በፍርድ ዕለት የደቡብ ንግሥት ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳርቻ መጥታለችና። እነሆ፤ ከሰሎሞን የሚበልጥ እዚህ አለ።

“ርኩስ መንፈስ ከሰው ከወጣ በኋላ ዕረፍት ለማግኘት ውሃ በሌለበት ደረቅ ቦታ ይንከራተታል፤ የሚሻውን ዕረፍት ግን አያገኝም። ከዚያም፣ ‘ወደ ነበርሁበት ቤት ተመልሼ ልሂድ’ ይላል፤ ሲመለስም ቤቱ ባዶ ሆኖ፣ ጸድቶና ተዘጋጅቶ ያገኘዋል። ከዚያም ይሄድና ከራሱ የባሱ ሌሎች ሰባት ክፉ መናፍስት ይዞ ይመጣል፤ እነርሱም ሰውየው ውስጥ ገብተው ይኖራሉ። የዚያም ሰው የኋለኛው ሁኔታ ከፊተኛው የከፋ ይሆናል። በዚህ ክፉ ትውልድም ላይ እንዲሁ ይሆንበታል።”

ኢየሱስ ለሕዝቡ ሲናገር ሳለ፣ እናቱና ወንድሞቹ ሊያነጋግሩት ፈልገው በውጭ ቆመው ነበር። አንድ ሰውም፣ “እነሆ፣ እናትህና ወንድሞችህ ሊያነጋግሩህ ፈልገው በውጭ ቆመዋል” አለው። ኢየሱስም፣ “እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነማን ናቸው?” ሲል መለሰለት። በእጁም ወደ ደቀ መዛሙርቱ እያመለከተ እንዲህ አለ፤ “እናቴና ወንድሞቼ እነዚህ ናቸው፤በሰማይ ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፣ ወንድሜ፣ እኅቴና እናቴም ነው።”

 

አስተንትኖ

የተወደዳችሁ የእግዚኣብሔር ቤተሰቦች እና በጎ ፈቃድ ያላችሁ ሁሉ!

 “እግዚአብሔር ለቍጣ የዘገየ፣ ፍቅሩ የበዛ፣ ኀጢአትንና ዐመፃን ይቅር የሚል፣ በደለኛውን ግን ሳይቀጣ የማይተው” አምላክ ነው ይለናል ዘኁልቍ 14:18። በሰላም ጠብቆን፣ መተላለፋችንን በትዕግስት አሳልፎ ለሠራናቸው ኃጢያቶች ሁሉ ይቅርታን እንጠይቅ ዘንድ ጊዜ ሰጥቶን፣ ተስፋ ስንቆርጥ ተስፋ ሆኖን፣ በምንፈራበትና  በምንሸበርባቸው ወቅቶች  ሁሉ አይዞህ/ አትፍራ/ በማለት ብርታትን ሰጥቶን ለዛሬው ቀን ያደረሰን እግዚኣብሔር ቅዱስ አባታችን  ስሙ የተመሰገነ ይሁን።እንደ ሚታወቀው እንደ አገራችን ሥርዓተ አምልኮና መንፈሳዊ ልማድ በእመቤታችን በኩል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ስለገለጠው ተስፋና በእርስዋም ጸጋ መሞላት ላደረገልን ቸርነት በተለየ ሁኔታ በየዓመቱ ለ16 ቀናት የሚዘለቀወን ጾምና ምህለላ የምናደርግበት የፍልሰታ ዘመን ላይ እንገኛለን። እግዚአብሔር አብ በእርሱ ለኖሩት ሁሉ ሊያደርግላቸው ቃል የገባውን እውነታ እርሱ በፈቀደው መልኩ በእመቤታችን የተገበረበትን ጸጋ እንወድሳለን፤ ለእኛም ይሆንልን ዘንድ “ማርያም ሆይ! ቸር፣ የሰው ልጆች ሁሉ አዳኝ ወደ ሆነው ልጅሽ ለምኝልን/ በማለት የእናትነት አማላጅነቷን በምንማጽንበት በዚህ የፍልሰታ ወቅት በጾም፣ በጸሎትና በምዕለላ እግዚኣብሔርን የምንማጸንበት እና መልካም ፍሬ የምናፈራበት ወቅት ሊሆን የገባል።

የዚህን አስተንትኖ ሙሉ ይዘት ከዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!

በዛሬው እለተ ሰንበት ቤተክርስቲያናችን እንድናስተነትን፣ በሕይወታችን ውስጥ በማስረጽ ጸጋ እና በረከት እንድናገኝ  ከእህት  ወንድሞቻችን ጋር በሰላም እንድንኖር  ይረዳን ዘንድ የሚከተሉትን ምንባባት ሰጥታናለች።

በዛሬው የመጀመሪያ ምንባብ ላይ ቅዱስ ሐዋሪያ ጳውሎስ ለጣዖት የተሠዋ ሥጋን በተመለከተ ሲናገር እንሰማለን። በዚያን ወቅት አረማዊያን ለጣዖቶቻቸው ሥጋን በመስዋዕትነት ካቀረቡ ቡኃላ የተረፈውን ሥጋ የጣዖቱ ካህናት፣ መስዋዕት አቅራቢውና ከእርሱ ጋር የነበሩ ሰዎች ይበሉታል ወይም ደግሞ ወደ ገበያ አውጥተው ይሸጡት ስለነበረ አንድ አንድ ክርስቲያኖች ደግሞ በዚህ መልክ የቀረበውን ሥጋ ገዝተው መብላት ጣዖትን እንደ ማምለክና በክርስቶስ ላይ ካላቸው እምነት እንደ አፈገፈጉ ይቆጠር ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ ለሌሎች ግን ያንን ሥጋ ገዝቶ መመገብ ምንም ችግር አያስከትልም የሚል ክርክር አስነስተው ስለ ነበረ ጳውሎስ ለዚሁ ክርክር መልስ ለመስጠት ፈልጎ የጻፈው መልእክት ነው።

ሐዋሪያው ጳውሎስ ለጣዖት የተሰዋ ሥጋ መብላት ምንም ጉዳት እንደማያመጣበት ቢያውቅም ደካማ የሆነ ወንድሙን የሚያሰናክል ነገር መስሎት ከታየው ግን ለዘለዓለም ሥጋ ሳይበላ መቆየት እንደ ሚመርጥ ይናገራል። ለጳውሎስ ዋናው ቁምነገር የነበረው ጉዳይ የመብላት እና ያለመብላት ጉዳይ ሳይሆን “ምግብ ወደ እግዚኣብሔር አያቀርበንም፣ ባንበላ የሚጎልብን ነገር የለም፣ ብንበላም የምናተርፈው ነገር የለም ይለናል። ለጳውሎስ በጣም አስፈላጊ የነበረው ቁምነገር ግን በምንም ዓይነት ሁኔታ የምናደርጋቸው ማንኛውም ዓይነት ድርጊቶች ለደካሞች ዕንቅፋት ሊሆን አይገባ የሚለው ነው። ስለዚህም ለወንድሞቻችን እና ለእህቶቻችን ዕንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ማንኛውንም ዓይነት ተግባሮቻችንን ማቆም ይኖርብናል ማለት ነው።

በወንጌል ውስጥ ኢየሱስ ይህንን በተመለከተ “ሰውን የሚያረክሰው ከአፉ የሚወጣው እንጂ ወደ አፉ የሚገባው አይደለም” (ማቴዎስ 15:11) በማለት ይናገራል። ነገር ግን ለማንም ሰው መሰናክል መሆን እንደ ማይኖርብን በሚገልጸው የኢየሱስ መልእክት ላይ “ይህ ሰው ከእነዚህ ከታናናሾች አንዱን ከሚያሰናክል፣ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ባሕር ቢጣል ይሻለው ነበር” (ሉቃስ 17:2) በማለት በምንም ዓይነት መልኩ ለሌሎች እንቅፋት መሆን እንደ ማይገባን ያስተምረናል።

በሁለተኛ ደረጃ በተነበበው ምንባብ ላይ ሐዋሪያው ጴጥሮስ “ከእንግዲህ በሚቀረው ምድራዊ ሕይወት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ምኞት አይኖርም። አሕዛብ ፈቅደው እንደሚያደርጉት በመዳራት፣ በሥጋዊ ምኞት፣ በስካር፣ በጭፈራ፣ ያለ ልክ በመጠጣት፣ በአስጸያፊ የጣዖት አምልኮ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል” ይህ እውነታ እኛ ዛሬ ባለንበት ዘመን በከፍተኝ ሁኔታ የሚታይ ተግባር ነው። ሰለዚህም እነዚህን ከንቱ የሆኑ ነገሮች በመተው፣ በተለይም በዛሬው ወቅት ጣዖታችን እየሆኑ የመጡትን ከልክ በላይ ገንዘብ እና ንብረት የማካበት ፍላጎቶቻችን ከእግዚኣብሔር መንገድ የሚያርቁን፣ እዚሁ ጊዜያዊ በሆነ ዓለም ጥለነው የምንሄደው ነገር በመሆኑ የተነሳ ዘላቂውን የእግዚኣብሔር ምሕረ በመሻት ተመጣጣኝ የሆነ የአኑኗር ዘይቤን በመከተል ካለን ለድኾች በማካፈል መኖር እንደ ሚገባን ሐዋሪያው ጴጥሮስ ዛሬ ያሳስበናል። በተጨማሪም ምድራዊ የሆነ ደስታን ብቻ ሊያጎናጽፉን የሚችሉ ተግባራትን በተለይም ደግሞ ከልክ በላይ የሆኑ ነገሮችን በቅድሚያ ለጤናችን ጥሩ ባለመሆናቸው የተነሳ፣ በማስከተል ደግሞ ከሰዎች እና ከራሳችን ጋር ብሎም ከእግዚኣብሔር ጋር ሊያጋጩን የሚችሉ የኃጢኣያት ምክንያቶች እንዳይሆኑብን ሁሉንም ነገሮች በመጠን ማድረግ ይገባናል ማለት ነው።    

የዛሬው ቅዱስ ወንጌል ውስጥ አንዳንድ የአይሁድ ሃይማኖት መምህራንና ፈሪሳውያን፣ “መምህር ሆይ፤ ከአንተ ተአምራዊ ምልክት ማየት እንፈልጋለን” ብለው ኢየሱስን በጠየቁት ጊዜ እርሱ ግን መልሶ  “ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክትን ይጠይቃል፤ ነገር ግን ከነቢዩ ዮናስ ምልክት በስተቀር ሌላ ምልክት አይሰጠውም” ይለናል። ፈሪሳዊያኑ ይህንን ጥያቄ ያነሱበት ምክንያት ኢየሱስ በእውነት መሲህ መሆኑንና አለመሆኑን ለመረጋገጥ ከነበራቸው ፍላጎት የመነጨ ሲሆን እርሱም በሰማይ ላይ ጉልህ በሆነ መልኩ የሚታይ ምልክት ለማየት ፈልገው ነበር። ነገር ግን ኢየሱስ ጥያቄአቸውን የመለሰው እነርሱ በፈለጉበት መንገድ ሳይሆን በታሪካቸው ውስጥ ስለተከሰተው አንድ ምልክት በመጥቀስ ነበር። ይህም “ይህ አመንዝራ ትውልድ” (ማቴ. 12:39) የሚለው ነው።

በዚህ በዛሬው ወንጌል ውስጥ የተጠቀሰው አመንዝራ የሚልው ቃል የሚያመልክተው መንፈሳዊ ባል ለሆነው እግዚኣብሔር የእርሱ ትውልድ ወይም ሕዝቦች ታማኝ ሆነው አለመገኘታቸውን ነው እንጂ በሥጋ ማምንዘርን አያመለክትም። ዛሬ ይህንን የቅዱስ ወንጌል ቃል በጥልቀት መመልከት እና ሕይወታችንን መመርመር ይኖርብናል። ዛሬም ቢሆን ኢየሱስ ጌታ መሆኑን በተለዩ ምክንያቶች ልንጠራጠር እንችል ይሆናል። ምናልባት ታመን በአልጋ ላይ በምንሆንበት ሰዓት በቶሎ ለመዳን ካለን ጉጉት የተነሳ እግዚኣብሔር ቅጽበታዊ በሆነ መልኩ እንዲያድነን በመሻት ምልክት እንፈልግ ይሆናል። ምናልባት ልባችን በዚህ ዓለም ሃብትና ምቾት አብጦ በመደንደኑ የተነሳ እግዚኣብሔር የለም አያስፈገኝም፣ በሃብቴ እና በራሴ ጉልበት መኖር እፈልጋለሁ በማለት በምድራዊ ነገሮች በመመካት እርሱ መኖሩን እና አለመኖሩን ለማመን ተጨባጭ ምልክት እንፈልግ ይሆናል።  በእነዚህ እነዚህን በመሳሰሉ ምክንያቶች ከእግዚኣብሔር በመራቅ ምድራዊ የሆኑ ነገሮችን በመመካት በምንኖርበት ወቅት በእግዚኣብሔር ላይ ላይ እናመነዝራለን ማለት ነው።

በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ እግዚኣብሔር ብዙ ምልክቶችን እንዳሳየ ተጠቅሶ እናገኛለን። ለምሳሌም ሙሴ እግዚኣብሔር ከሁሉም አማልክት በላይ መሆኑን ለፈርዖን ለማሳየት በፈለገበት ወቅት እግዚኣብሔር ታላላቅ የሆኑ ተአምራትን ማድረጉን እንውቃለን። ሙሴ በዚሁ ተግባሩ እግዚኣብሔር ከሁሉም በላይ እንደ ሆነ፣ በዚህ ምድር ካሉ ነገሮች ሁሉ የሚስተካከለው ወይም የሚወዳደረው እንደሌለ ለፈርዖን አሳይቱዋል። ይህንምም ያደርገው እጁን በባሕር ላይ በዘረጋበት ወቅት ባሕሩ ለሁለት ተከፈለ እግዚኣብሔር የሁሉም የበላይ መሆኑን አሳየ። በዚሁ መልኩ በእግዚኣብሔር ኃይል እየተመራ ሕዝቡን ከባርነት ነጻ አወጣ።

በአንጻሩ ግን ኢየሱስ ወደ ዚህ ምድር የመጣው እስራኤላዊያን እንዳሰቡት ከሮማዊያን ቅኝ ግዛት ሊያወጣቸው ፈልጎ ሳይሆን የመጣው ነገር ግን የዚህ ዓለም የሞት ምንጭ የሆነውን ኃጢያትን ድል ለማድረግና  እያንዳንዱ ሰው ንስሐ በመግባት መንፈሳዊ ለውጥ በማምጣት በእምነት እና በእርሱ ቃል በመመመራት ኃጢያትን ያሸንፍ ዘንድ ሊያበቃቸው ነው የመጣው። እርሱ በመንፈስ ቅዱስ ከቅድስት ድንግል ማሪያ መወለዱ፣ በሽተኞችን ማዳኑ ከተቸገሩት ጋር አብሮ መቸገሩ በራሱ ከእግዚኣብሔር ዘንድ የመጣ መሆኑን ያረጋግጣሉ። ነገር ግን እርሱ ያሳየቸው የነበሩ ምልክቶች ዓለም እንደ ሚፈልገው ዓይነት ታላቅነቱን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሳዩ ምልክቶችን ሳይሆን ያሳይ የነበረው ነገር ግን በታላቅ ትህትናና ንጹህ በሆነ መልኩ ፍቅሩን አሳይቶናል። በፍቅር ታላላቅ ተግባራትን በመፈጸም እግዚኣቤሔር ከእርሱ ጋር እና እርሱ ከእግዚኣብሔር ጋር መሆኑን አሳይቱዋል ዛሬም ቢሆን እያሳየ ይገኛል።

በተጨማሪም ኢየሱስ አባቱ እና እናቱ እንዲሁም ወንድሞቹ እና እህቶቹ ሊሆኑ የሚችሉ ሰዎች የእርሱን ቃል ሰምተው በተግባር የሚያውሉ ሰውች ብቻ መሆናቸውን በመግለጹ ታላቅ መሆኑ አሳይቱዋል። ወገንተኛነቱን የገለጸው የእርሱን ቃል ሰምተው በተግባር የሚያውሉ ሰዎች መሆናቸውንም በተግባር አሳይቶናል።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንዲሁም በጎ ፈቃድ ያላችሁ ሁሉ!

በዛሬው ሰንበት ቀን እግዚሐብሔር በእየለቱ በሕይወታችን ውስጥ እያከናወነ የሚገኘውን ምልክቶች በመረዳት፣ በዚህ ዓለም በምንኖርበት ወቅት በመጠን እንድንኖር እንዲረዳን፣ ለወንድሞቻችን እና ለእህቶቻችን እንቅፋት ሳንሆን በመልካም አብነት እንድንመራቸው እና ወደ እግዚኣብሔር ቤት እንድናቀርባቸው የሚያስችለንን መንፈሳዊ ለውጥ እንድናመጣ በጸጋው እንዲረዳን፣ የእርሱን ቃል ሰምተን በተግባር ላይ በማዋል ፍሬያማ የሆነ ሕይወት እንድንኖር ይረዳን ዘንድ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማሪያም አማላጅነት ልንማጽነው ይገባል።

 የሰማነውን በልቦናችን ያሳድርልን። አሜን! 

በአባ መብራቱ ኃይለጊዮርጊስ የተዘጋጀ። 

 


"እምነት የሕይወት ጉዞዋችንን የሚደግፍ ነገር ነው እንጂ የማምለጫ መንገድ ወይም የመሸሸጊያ ዋሻ አይደለም"

$
0
0

ዘወትር እሁድ እለት ምዕመናን፣ ነጋዲያን እና የሀገር ጎብኚዎች በቫቲካን በሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ አማካይነት በእለቱ በሚነበበው የቅዱስ ወንጌል ቃል ላይ ተመርኩዘው የሚሰጡትን  አስተንትኖ ለመከታተል እንደ ሚሰበሰቡ ይታወቃል።

የዚህን ዜና ሙሉ ይዘት ከዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!

የዚህ መርዕ ግብር አንዱ አካል በሆነው በትላንትናው እለት ማለትም በነሐሴ 7/2009 ዓ.ም. ቅዱስነታቸው ያደረግት አስተንትኖ መሰረቱን አድርጎ የነበረው በእለቱ በላቲን ስርዓተ አምልኮ አቆጣጠር ደንብ መሰረት ከማቴዎስ ወንጌል 14:22-33 በተወሰደው እና ኢየሱስ በባሕር ላይ እየተራመደ መሄዱን በሚገልጽው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ላይ ያተኮረ እንደ ነበረም ለመረዳት የተቻለ ሲሆን “እምነት የሕይወት ጉዞዋችንን የሚደግፍ ነገር ነው እንጂ የማምለጫ መንገድ ወይም የመሸሸጊያ ዋሻ አይደለም” ማለታቸው ታውቁዋል።

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጵሳት ፍራንቸስኮ በትላንትናው እለት በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ያደረጉትን አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል እንድትከታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!

ዛሬ (ከማቴዎስ ወንጌል 14:22-33) በተነበበው ቃል ላይ ኢየሱስ ሌሊቱን ሙሉ ሲጸልይ ካመሸ ቡኃላ  በገሊላ ባሕር ላይ እየተራመደ ደቀ መዛሙርቱ  ወደ አሉበት በጀልባ መሄዱን ይገልጻል። በዚያ ጊዜ ጀልባዋ ባሕሩን ዘልቃ እየተጓዘች ሳለች ነፋስ ተነሥቶ በማዕበል ትንገላታ ጀመር። ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስ በባሕሩ  ላይ እየተራመደ ሲመጣ ባዩት ጊዜ ፈሩ፤ እነርሱም፣ምትሀት ነው!” በማለት በፍርሃት ጮኹ! ኢየሱስም ወዲያውኑ፣ “አይዞአችሁ፤ እኔ ነኝ አትፍሩ” አላቸው። ጴጥሮስም፣ ከጀልባው ወርዶ በውሃው እየተራመደ ወደ ኢየሱስ አመራ። ነገር ግን የነፋሱን ኃይል ባየ ጊዜ ፈራ፤ መስጠምም ሲጀምር፣ጌታ ሆይ፤ አድነኝ!” ብሎ ጮኸ። ኢየሱስም ወዲያውኑ እጁን ዘርግቶ ያዘውና ከመስመጥ አዳነው።

ይህ የወንጌል ክፍል ትርጉም ያለው ተምሳሌት የተካተተበትና በግለሰብ ደረጃ ይሁን እንደ ቤተክርስቲያን ማኅበረሰበ ስለእምነታችን እንድናሰላስል የሚያደርገን ነው። ይህ የኅብረተሰብ ክፍል ወይም ይህ የቤተክርስቲያን ማኅበረሰብ እምነት አለው ወይ? በእያንዳንዳችን እና በማህበረሰባችን ውስጥ ያለው እምነት እንዴት ነው? በዛሬው ወንጌል ውስጥ የተጠቀሰው ጀልባ የእያንዳንዳችንን እና የቤተክርስቲያን ሕይወት ያመለክታል፣ ብርቱ የነበረው አውሎ ንፋስ ደግሞ ተግዳሮቶቻችንን እና ፈተናዎቻችን ያመለክታል። ጴጥሮስም ኢየሱስን ጌታ ሆይ፤ በውሃው ላይ እየተራመድሁ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝያለው እና ከዚያም በመቀጠልጌታ ሆይ አድነኝ!” በማለት የተናገራቸው ቃላት እኛ ጌታ ቅርባችን ይሆን ዘንድ ከምንመኘው ምኞት ጋር ይመሳሰላል፣ እንዲሁም በራሳችን እና በማኅበረሰባችን ሕይወት ውስጥ የሚያጋጥሙንን ውስጣዊ እና ውጫዊ ፍርሃት እና ጭንቀቶች ያስታውሰናል።

ኢየሱስ ለጴጥሮስ የተናግራቸው እርግጠኛ የሆኑ ንግግሮች ብቻ በቂ አልነበሩም፣ ነገር ግን ለእርሱ በወቅቱ አስፈላጊ የነበረ ጉዳይ ቢኖር ኢየሱስ እጁን ዘርግቶ ይዞ ያዳነው ክስት ነው። ይህም በእኛ ሕይወት ውስጥ ሊከሰት የሚችል ነገር ነው። መተማመኛ ለማግኘት እና እርግጠኛ ለመሆን ያስችለን ዘንድ የእግዚኣብሔርን ቃል የሙጥኝ ብለን የማንይዝ ከሆነ እኛም መስመጥ እንጀምራለን ማለት ነው። የዛሬው ወንጌል በጌታ እና በቃሉ ማመን ሁሉም ነገር ቀላልና መረጋጋት ወይም ጸጥታ ባለበት መንገድ መራመድ ማለት እንዳልሆን ያስታውሰናል፣ እንዲሁም የሕይወትን ማዕበል ሁሉ ለማስወገድ የሚችሉ ነገሮች እንዳልሆኑም ያስታውሰናል።

እመነት ኢየሱስ ከእኛ ጋር እንደ ሆነ እርግጠኛ እንድንሆን ያደርገናል፣ ሕልውናችንን እንዳናጣ ያደርገናል፣ በችግርች ውስጥ በምንሆንባቸው ጊዜያት ሁሉ በመከራዎቻችን ብዛት የተነሳ እንዳንሰምጥ እጁን ዘርግቶ እንደ ሚረዳን ማረጋገጫ በመስጠት ጨለማ በሚባልበት ስፍራውስ ውስጥ እንኳን ቢሆን መንገድ ያሳየናል።  ባጠቃላይ እምነት በሕይወት ውስጥ ከሚያጋጥሙን ችግሮቻችንን የምንሸሸግበት ቦታ ሳይሆን ነገር ግን ይህንን መከራ እና ችግሮቻችንን እንድንወጣ በማድረግ ትርጉም ያለው ሕይወት እንድንኖር ያደርገናል።

አንድ ጀልባ ረጅም የሆነ ባሕርን በምያቋርጥበት ወቅት ጉዞ ላይ እያለ ጠንካራ የሆነ አውሎ ነፋስ ይገጥመዋል ይህም ክስተት ለአደጋ ያጋልጠዋል።  ይህ ክስተት በሁሉም ዘመናት ውስጥ የቤተክርስቲያን እውነታ የሚያሳይ ድንቅ የሆነ ምስል ነው። ቤተክርስቲያንን እስከ ዛሬ ቀን ድረስ ያዳናት በውስጡዋ የሚገኙ ሰዎች ብርታት ወይም ጥራት አይደለም፣ ቤተክርስቲያን አስቸጋሪ የሆነ ማዕበልን መወጣት የቻለችሁ ግን በክርስቶስ እና በቃሉ በተሰጣት ማረጋገጫ ነው፣ ይህም ማረጋገጫ በኢየሱስ እና በቃሉ ማመን ነው።

በዚህ ዓይነቱ ጀልባ ላይ በምንሳፈርበት ወቅት እርግጠኞች እንሆናለን፣ በተለይም ደግሞ በመከራዎቻችን እና በድክመቶቻችን ወቅቶች ሁሉ ልክ ደቀ መዛሙርቱ በስተመጨረሻበእርግጥ አነተ የእግዚኣብሔር ልጅ ነህ”! ብለው ለኢየሱስ እንደ ሰገዱለት ሁሉ እኛም ደግሞ ለኢየሱስ መንበርከክ እና መስገድ ይገባናል። ኢየሱስን በእርግጥ አነተ የእግዚኣብሔር ልጅ ነህ”! ማለት እንዴት ደስ የሚያሰኝ ቃል ነው? እስቲ ሁላችንም በጋራበእርግጥ አነተ የእግዚኣብሔር ልጅ ነህ”! እንበለው።

እመቤታችን ቅስት ደንግል ማሪያም በሕይወት ውስጥ የሚገጥሙንን ውጣው ውረዶችን በመቋቋ፣ በእመንት ጸንተን እንድንኖርና ምቀኝነትን ሆነ ስሜታዊነትን፣ የእራሳችንን ፍልስፍናዎች፣ ልምዶች እና መፈክሮች አስወግደን ቤተክርስቲያን ጀልባ ላይ ሆነን መጓዝ እንችል ዘንድ በአማልጅነቷ ትርዳን።

 

ከቫቲካ ሬዲዮ የአማሪኛ የስርጭት ክፍል የተላለፈው የእሁድ የነሐሴ 07/2009 ዓ.ም. ሙሉ ዝግጅት።

$
0
0

ከቫቲካ ሬዲዮ የአማሪኛ የስርጭት ክፍል የተላለፈው የእሁድ የነሐሴ 07/2009 ዓ.ም. ሙሉ ዝግጅት።

የዚህን ዝግጅት ሙሉ ይዘት ከዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!

ቅዱስ ኣባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ፥ በማርያም ውስጥ ትህትና የብርቱዎች ምግባር መሆኑ እንመለከታለን

$
0
0

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ትዊተር በተሰየመው ማኅበራዊ መረብት ዘንድ ባለው @Pontifex የግል አድራሻቸው በኩል እንደ ወትሮው የሚያስተላልፉት ቃለ ምዕዳን በመቀጠል እሁድ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም.  (ነሐሴ 7 ቀን 2009 ዓ.ም.) በማርያም፥ ብርቱዎች መሆናቸው እንዲሰማቸው ሌሎችን ማሰቃየት ሳይሆን ሰብአዊነት ደግነትና ትህትና የብርቱዎች ምግባር መሆኑ እናስተውላለን፡ እንዳሉ የቅድስት መንበር የዜናን ኅትመት ክፍል መግለጫ አመለከተ።

ቅዱስ አባታችን ያስተላለፉት ቃል የወንጌል ሃሴት በሚል ራስ ሥር በደረሱት ሐዋርያዊ ምዕዳን እንዲሁም ባለፈው እ.ኤ.አ. 2016  ግንቦት ወር በፖርቱጋል ዝክረ 100ኛው ዓመት ግልጸተ ማርያም በፋጢማ ምክንያት በቅድስተ ማርያም ዘፋጢማ ቅዱስ ሥፍራ ወደ ሚገኘው የግልጸተ ማርያም ቤተ ጸሎት መንፈሳዊ ንግደት ባከናወኑበት ወቅት አስተላልፈዉት የነበረውን መልእክት አስተንፍሶ ያደረግ መሆኑ የገለጠው የቅድስት መንበር የዜናና ኅትመት ክፍል መግለጫ አክሎ፡ ቅዱስነታቸው ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. በግልጸተ ማርያም ቤተ ጸሎት ተገኝተው፥ ከክርስቶስና ከማርያም ጋር እኛ በእግዚአብሔር ዘንድ እንሆናለን፡ ክርስቲያን ለመሆን ከፈለግን ማርያማውያን መሆን ይገባናል። ማለትም ማርያምንና ኢየሱስን የሚያስተሳስረው ወደ ኢየሱስ የሚመራን መንገድ የሚከፍት አስፈላጊው ህያው እና የእግዚአብሔር ኣሳቢነት የሚያረጋግጥ በመካከላቸው ያለው ግኑኝነት እውቅና መስጠት ይገባናል እንዳሉ በማስታወስ ይጠቁማል።

ቅዱስነታቸው በግልጸተ ማርያም ዘፋጢማ ቤተ ጸሎት፥ ማርያም፥ የመንፈሳዊ ሕይወት መምህር፥ ኢየሱስን በዚያ አስጨናቂ በሆነው በመስቀል መንገድ ለእኛ አብነት ለመሆን የተከተለች ቀዳሜ የእርሱ ተከታይ ነች፡ “ዘወትር በሁሉምና በማንኛውም ሁኔታ ስላመነች ብጽእት ነች፡ (ሉቃስ 1,42,45 ተመል.)። ወንጌላዊ ሓሴት ሐዋርያዊ ምዕዳን፥ “በየትኛውም ጊዜና ሁነት ማርያም ስንመለከትና የዋህነትና አሳቢነት ግብታዊ ኃይል እንዳለው ወደ ማመን ከፍ እንላለን፥ ትሕትና የዋህነት ኃይለ ልዕልናውንና የገዛ ኃይሉን ለማሳየት ሌሎችን ለመጉዳት ለሚል የሚሻው እንደሚመለከተው ድካምነት ሳይሆን የብርቱዎች መልካም ምግባር ነው፡ ይኽ የፍትህና የየዋህነት አስተንትኖ እና ወደ ሌሎች የማቅናት ሂደትም ነው፡ (ሓዋርያዊ ምዕዳን፥ ወንጌላዊ ሐሴት, 288 ቁጥር ተመል.)። እያንዳንዳችን በማርያም እና ከማርያም ጋር የዚያ ዘወትር ሁሉንም የሚምር የእግዚአብሔር ምሕረት ትእምርትና ምስጢር ይሁን እንዳሉ የቅድስት መንበር የዜናና ኅትመት ክፍል መግለጫ በማስታወስ ያመለክታል።

ደቡብ ሱዳን፥ ብፁዕ አቡነ ኩሳላ፥ የጋራ ውይይት እንዲረጋገጥ ከህዝብ ጎን ለመሆን የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት

$
0
0

ባለፉት የመጨረሻ ወራቶች በደቡብ ሱዳን የእርስ በእርስ ግጭት እልባት እንዲያገኝ ተደርሶ የነበረው የቶክስ አቍም ስምምን ጥሰት ተከትሎ እየታየ ያለው ፖለቲካዊ ውዝግብ በአገሪቱ ያለው ሁኔታ እጅግ የተወሳሰበና የከፋ እንዲሆን እያደረገ መሆኑ የቫቲካን ረዲዮ ጋዜጠኛ ፈደሪኮ ፒያና አስታወቁ።

የጦርነቱ ምክንያት ፖለቲካዊ ሳይሆን ጎሳዊና ባህላዊ ነው ሲሉ የሱዳይ የቶምቡራና ያምቢዮ ሰበካ ጳጳስ የአገሪቱ ብፁዓን ጳጳሳት ጉባኤ ሊቀ መንበር ብፁዕ አቡነ ኤድዋርድ ሂቦሮ ኩሳላ ከቫቲካን ረዲዮ ጋር በስልክ ባካሄዱት ቃለ ምልልስ ገልጠዋል።

እኛ የምንፈልገው ይላሉ ብፁዕነታቸው፥ ደቡብ ሱዳን እንደ አገር የሚያጸናት ስምምነት ሰላም ፍትህ እንዲረጋገጥ እንጂ የአገሪቱን ሕዝብ ጨርሶ ኑሮውን እንዲያሻሽል የማያደርገው የፖለቲካው ሥልጣንና የአገሪቱን ሃብት ለመቆጣጠር የሚደረግ ፍጥጫና የርእስ በእርስ ግጭት አይደለም

በማለት ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ሱዳንን ለመጎብኘት ያላቸው ፍላጎት ገሃድ አድርገዋል። ሆኖም በአገሪቱ ምድር ላይ ያለው ሁኔታ ግምት በመስጠት ሐዋርያዊ ጉብኝቱን እ.ኤ.አ. በዚህ በ 2017 ዓ.ም. ይከወናሉ ብሎ ለመናገሩ የሚያዳግት ቢሆንም በደቡብ ሱዳን የምትገኘው ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ግብኝቱ እንዲከናወን የሚያስችሉ ሁኔታዎች እንዲረጋገጡ በማድረጉ ረገድ አቢይ ጥረት እያከናወነች እንደምትገኝ ገልጠው ተስፈኛም ነች ብሏል።

አሁንም ቢሆን በደቡብ ሱዳን ያለው ሁኔታ እጅግ የከፋ ነው። ምንም’ኳ የሰላም ውይይት ቢከናወንም በመንግሥት ወታደሮችና አማጽያኑ መካከል ግጭቱ አልረገበም ጦርነቱም እልባት አላገኘም፡ የዚህ ጦርነት ሰለባም ንጹሓን ዜጎች ናቸው። በደቡብ ሱዳን ስቃይና ችግር የማይታይበት ክልል አንድም የለም ምክንያቱም ጦርነቱ እንደ ወረርሽኝ በሁሉም ክልል እየተዛመተ ነው፡ ይኽ ደግሞ ለሚሰቃየው ሕዝብ መሰረታዊ ፍልጎቶቹን ለማርካት በሰብአዊ እርዳታ ለማቅረብ የሚያስችሉ መርሃ ግብሮች ለመከወን አዳጋች እንዲሆን እያደረገ ነው። የቤተ ክርስቲያን አቋም የሰላም መሣሪያ በመሆን ሰላምና እርቅ እንዲረጋገጥ ማድረግ የሚል የግብረ ገብና ድምጽ ለሌለው ድምጽ በመሆን የሰላም ውይይት በማረጋገጥ የአገሪቱና የሕዝቡ ጥቅም መረጋገጥ አለበት የሚል ነው፡ ሆኖም ለዚህ ለምታደርግው ጥረት ከማንኛውም አካል አወንታዊ ምላሽ አልስተሰጠበትም ይላሉ።

በደቡብ ሱዳን ያለቸው ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ታጣቂ ኃይሎች ከመንግሥት ጋር እንዲደራደሩ ለመገፋፋት ተጨባጭ ተግባሮችን እያከናወነች ትገኛለች። ጦርነቱ እስካለ ድረስ የአገሪቱ መንግሥት የሕዝብ መሰረታዊ ፍላጎት ለማርካትም ሆነ የአገልግሎት መስጫ ተቋሞች የተሟላ ለማድረግ አይቻልም። በሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት ቤተ ክርስቲያን ቀዳሚው ሥፍራ ይዛ ብትገኝም ረጅ አካላት የክልሉ ጦርነት ቀጣይ በመሆኑ ምክንያት እያሰለቻቸው ያለ ይመስላል፡ ያአገሪቱ መንግሥትና ታጣቂ ኃይሎች ጦርነቱን ለማቆም ፍላጎት ያላቸው መሆን ይገባቸዋል። ይኽ ጦርነት ለመግታት የሚለው ፍላጎት ጦርነቱ እልባት እንዲያገኝ ለሚደረገው ጥረት ውሳኝ ነው፡ ካልሆነ የርእር በእርሱ ጦርነት ለማስወገድ አይቻልም ብሏል።

ሕዝቡ ምግብም ሆነ የሕይወት ደህንነት እንዲያገኝም መጠለያ ለማግኘት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይጎርፋል። ቤተ ክርስቲያን አብራው የስቃዩ ተካፋይ በመሆን የሰላም ጥሪ ከማቅረብ አልቦዘነችም ዘወትር ከሚሰቃየው ሕዝብ ጋር ነች በማለት ያካሄዱት ቃለ ምልልስ አጠቃሏል።

የካቶሊካዊ ተሃድሶ እንቅስቃሴ አጀማመርና ዓላማ ክፍል 9 አስተምህሮ በክቡር አቶ ዩሐንስ መኮንን

$
0
0

የካቶሊካዊ ተሃድሶ እንቅስቃሴ ክፍል 9

እንደሚታወቀው ካቶሊካዊ ተሃድሶ እንቅስቃሴ፣ ምዕመናን በያሉበት ሥፍራ ሆነው በምስጢረ ጥምቀት ጸጋ አማካይነት የተቀበሉት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ፣ ሐዋርያው ጳውሎስ እንደሚለው፣ ተዳፍኖ ወይም ተዳክሞ እንዳይቀር በጋራ ጸሎት፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ኃይልን እንዲያገኙ የሚያስተባብርና የሚመክር እንቅስቃሴ ነው። ይህ በመሆኑ ከብዙ ዓመታት ወዲህ ከርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከጳጳሳት፣ ከካህናትና ከምዕመናን የተለያዩ መንፈሳዊና ቁሳዊ ድጋፍን ሲያገኝ ቆይቶአል፣ በማግኘትም ላይ ይገኛል። ባለፉት ዝግጅቶቻችን የሁለቱን የቀድሞ ርዕሳነ ሊቃነ ጳጳሳት ማለትም የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ጳውሎስ ስድስተኛ እና የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ ለካቶሊካዊ ተሃድሶ እንቅስቃሴ የላኩትን የማበረታቻ መልዕክቶችን ማቅረባችን ይታወሳል። በዛሬው ዝግጅታችን የቀድሞ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክት 16ኛ፣ ለእንቅስቃሴው አባላትና አስተባባሪዎች የላኩትን ሐዋርያዊ መልዕክት እናቀርባለን።

የዚህን አስተምህሮ ሙሉ ይዘት ከዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!

“በአዲስ ኪዳን መጽሐፍ ውስጥ ተጽፎ የምናገኘው፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ሐዋርያት ለጸሎት በተሰበሰቡበት ሥፍራ መንፈስ ቅዱስ በእያንዳንዳቸው ላይ የመውረዱ ሁኔታ በታሪክ መልክ በየጊዜው እየተነገረ የሚዘልቅ አንድ አጋጣሚ ብቻ ሳይሆን ያው አንዱ መንፈስ ቅዱስ እስከ ዛሬ ድረስ በቤተክርስቲያን ላይ እየወረደ መሆኑ እና ወደ ፊትም ሳያቋርጥ እንደሚወርድ መዘንጋት የለብንም። ይህ የቤተክርስቲያን ሕይወት የሆነው እና አምላካዊ ኃይል ያለው መንፈስ ቅዱስ በዘመናት ሁሉ እንዲሁም በዘመናችንም የሚያስደንቁ ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን በግልጽ የምናየው ነው። በካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ እንቅስቃሴዎችና ማኅበራት እየተበራከቱ መምጣት በእርግጥም መንፈስ ቅዱስ በቤተክርስቲያንና በኅብረተሰባችን ላይ መውረዱን እንዳላቋረጠ ያረጋግጥልናል።” በማለት እ.አ.አ ጥቅምት ወር 2008 ዓ.ም. በሮም ለተሰበሰቡት ካቶሊካዊ ተሃድሶ እንቅስቃሴ አባላት ሐዋርያዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ነበር። ቀጥሎም እ.አ.አ ግንቦት ወር 2012 ዓ.ም. ባስተላለፉት ሐዋርያዊ መልዕክታቸው “ውድ በመንፈስ ቅዱስ የመታደስ እንቅስቃሴ አባላት በሙሉ፥ መላው ዓለም ከምን ጊዜም በላይ የእናንተን የጸሎት እገዛ ይፈልጋል። ምድራዊውን ሳይሆን ሰማያዊውን ጸጋ በመመኘት ወደ እግዚአብሔር ምስጋና የሚያቀርቡትን ሰዎች ጸሎት ይፈልጋል፤ ዘወትር ደስ ይበላችሁ፤ የተሃድሶ እንቅስቃሴአችሁ እንዲያድግና እንዲስፋፋ ወደ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዘንድ አደራ እላለሁ። ከእርሷ ጋር በጸሎት ተባበሩ። ከመንፈስ ቅዱስ በምታገኙት ብርሃን በመመራት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ለዓለም አብስሩ።” ማለታቸው ይታወሳል።

የክርስትና ሕይወታችን በውስጣችን ሕይወትን የሚያገኘው ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ነው። አዲስ ሕይወት ማለትም አብንና ከእርሱ የተላከውን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ማለት ነው። በዮሐ. ወንጌል ምዕ. 17 ቁጥር 3 ላይ እንዲህ የሚል ተጽፎአልና፥ “የዘለዓለም ሕይወትም፣ ብቻህን እውነተኛ አምላክ የሆንከውን አንተንና የላክኸውን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ነው።” መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር አብሮአቸው ስለሚኖር ኢየሱስ ክርስቶስን የምናምን ሁላችን መንፈስ ቅዱስንም እናምናለን እናውቀዋለንም። ስለዚህ እንደ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት በነዲክት 16ኛ ሐዋርያዊ መልዕክት መሠረት ሰላምና ፍቅር ለጎደለው፣ ርኅራሄና ኅብረት ለጎደለው ለዚህ ለምንኖርበት ዓለም የመንፈስ ቅዱስን እርዳታ አጥብቀን በኅብረት መለመን ያስፈልጋል።

የተወደዳችሁ አድማጮቻችን ካቶሊካዊ ተሃድሶ እንቅስቃሴን በማስመልከት ያቀረብነውን ዝግጅት በዚህ እንፈጽማለን። ሳምንት በተመሳሳይ ርዕስ እስክንገናኝ ከመንፈስ ቅዱስ የሚገኝ ሰላምና ፍቅር እንዲሁም አንድነት ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን።

በአቶ ዮሐንስ መኰንን የተዘጋጀ

 

የካቶሊክ እምነታችን ምንነት ከፍል 1 አስተምህሮ

$
0
0

የካቶሊክ እምነታችን ምንነት

  1. ለምን ቤተክርስቲያናችንን ካቶሊካዊት እንላታለን?

“ካቶሊክ” ማለት አጠቃላይ፣ ዓለም አቀፋዊ፣ ለሁሉም ሰውና ለሁሉም ዓለም የሚሆን ማለት ነው። ስለሆነም ቤተክርሲያናችን ሁሉንም ዓለም፣ ሁሉንም ሀገር፣ ሁሉንም ዘር፣ ሁሉንም ባህልና፣ ሁሉንም ትውልድ የምያቅፍ ስለሆነች ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እንላታለን።

  1. ለምንድነው የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን ሮማዊት የምንለው?

ቤተክርስቲያናችን ሮማዊት ነች፣ ምክንያቱም የቤተክርስቲያናችን የመጀመሪያ እረኛ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮማ ስለኖረ፣ ስለሞተና በዚያው ስለተቀበረ ነው። ቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ነው። አሁኑም ታዲያ የሮም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ልክ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ የመላው የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የበላይ እረኛ ነው። እርሱ የክርስቶስ ተከታዮችን በአንድ ላይ የሚጠብቅና የመላው ቤተክርስቲያን አንድነት ምሳሌ ነው። በሮም ያለው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳችን ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን የመሠረተበት የቅዱስ ጴጥሮስ ዓለት ነው። ከዚህ እረኛዋ ጋር ሆና በምታደርገው ትግል ቤተክርስቲያን ምን ጊዜም የዓለም ኃያላት ሊያሸንፋት አትችሉም፣ ይህ ደግሞ ክርስቶስ ራሱ የገባላት ቃል ነው (ማቴ. 16,18)።

  1. ለምንድነው ቤተክርስቲያናችን አንዲት ናት እንላለን?

ቤተክርስቲያናችን አንዲት ናት የምንልበት በርካታ ምክንያቶች አሉን።

  1. ከሰው ዘር ሁሉ የተውጣጡ በመላው ዓለም የሚገኙ ካቶሊካዊያን ሁሉ እኩል የሚያከብሩትና የሚናገሩት አንድ ቅዱስ ቁርባን ያላት በመሆኑ የተነሳ ነው። በዚህ እጅግ ቅዱስ በሆነው ምስጢር አማካይነት ክርስቶስ በዚህ ማዕዱ ዙሪያ እንደ አንድ ቤተሰብ ስብስቦን በግልጽ የሚያስተሳስረን እስርሱ ነው።

  2. እኛ ካቶሊኮች በዓለም ዙሪያ ሁሉ ተመሳሳይ የአምልኮ ስርዓት ያለን ሲሆን ካቶሊኮች ሁሉ ከሮም ጳጳስ ጋር በጠበቀ እምነት ሲኖሩ ምን ጊዜም በማንኛውም የተሳሳተ አስተምህሮ ሳይነቃነቁ ከጴጥሮስ ዓለት ጋር በፍጹም አንድነት ይኖራሉ። (የካቶሊክ እምነታችንን ምንነት ግጽ 12) ራዲዮ ቫቲካን --የሰማ ላልሰማ ያሰማ!

4. የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለምንድነው ሐዋሪያዊት ተብላ የምትጠራው?

የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን “ሐዋሪያዊት” ነች ብለን የምንጠራበት ሁለት ዋነኛ ምክንያቶች አሉ፣

በመጀመሪያ ደረጃ ባልተቆራረጠ ሰንሰልት ከሐዋሪያት ዘመን ጀምሮ በጳጳሳትና በአቡናት መተካካት እስከ ዛሬ ድረስ የዘለቀች በመሆኗ ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ቤተክርስቲያናችን በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እና በአቡናት አመራር ሥር ሆና የሐዋሪያትን ትምህርትና እምነት የምትኖር፣ የምታስተምርና የምትጠብቅ በመሆኗ የተነሳ ነው።

5. ለምንድነው የካቶሊክ ቤተክርስቲያናችንን ቅድስት ናት ብለን የምንጠራው?

ቤተክርስቲያን ማለት የእግዚኣብሔር ሕዝቦች የሚሰበሰቡበት ቦታ ማለት ነው፣ የጌታ የሆኑ ሁሉ ማለትም ነው። ቤተክርስቲያንን ቅድስት የሚያደርጋት ጌታ ራሱ ነው። እርሱ ሙሽራው ሙሽራይቱን እንደሚወድ ቤተክርስቲያንን ይወዳታልና። እኛ ካቶሊኮች ኃጢያተኛ መሆናችች እንናዘዛለን፣ ነገር ግን የክርስቶስ ፍቅር እንደ ሚቀድሰንና የቅድስት ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አካል እንደ ሚያደርገን እንናገራለን/እናውጃለን።

ምንጭ፣-የካቶሊክ እምነታችንን ምንነት፣ የኢትዮጲያ ካቶሊካዊት ጠቅላይ ጽህፈት ቤት ሐዋሪያዊ ሥራዎች ኮሚሽን በ2007 ዓ.ም. ካሳተመው መጽሐፍ ከገጽ ግጽ 11, 12 የተወሰደ!

 

የካቶሊክ እምነታችን ምንነት ከፍል 2 አስተምህሮ

$
0
0

የካቶሊክ እምነታችን ምንነት ከፍል 2 አስተምህሮ

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ታዳሚዎች የካቶሊክ እምነታችን ምንነት፣ በካቶሊክ እምነትና ባህል ውስጥ የምናደርገው ቤተሰባዊ ጉዞ በሚል አርእስት የኢትዮጲያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽህፈት ቤት ሐዋሪያዊ ሥራዎች ኮሚሽን ካሳተመው መጽሐፍ ላይ ያገኘውን አስተምህሮ በተከታታይ ወደ እናንተ በማቅረብ ላይ እንገኛለን። እነሆ በዛሬው እለት ዝግጅታችን ደግሞ “እኛ ካቶሊኮች በሮም ያለውን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትን እንደ የጴጥሮስ ተተኪና የቤተክርስቲያናችን ራስ አድርገን ለምን እንደ ምንቀበል አጠር ባለ መልኩ ምክንያቶቹን እናቀርብላኃለን አብራችሁን ቆዩን።

ቅዱስ ጴጥሮስ የመጀመሪያው የሮም ጳጳስ ነው።

ቅዱስ ጴጥሮስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያኑን የመስረተበት ዓለት ነው። (ማቴ. 16:18)። ቅዱስ ጴጥሮስ የሐዋሪያት ሁሉ እንደራሴ እንደመሆኑ የመላይቱ ቤተክርስቲያን ራስ/የበላይ ነው። ኃላፊነቱ ክርስቶስ 3 ጊዜ ደጋግሞ እንዳስጠነቀቀው የክርስቶስን መንጋ መጠበቅ ነው (ዩሐንስ 21:15-17)። ቅዱስ ጴጥሮስ ስለ ክርስቶስ ሲል በንጉሥ ኔሮን ዘመን መንግሥት በሮም ከተማ በሰማዕትነት ሞቷል (በ64 ወይም 67 ዓ.ም.) የሞተውም እንደ ክርስትስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የነበረ ሲሆን የተሰቀለው ግን ከክርስቶስ ስቅለት በተቃራኒው ጭንቅላቱን በማዘቅዘቅ ነበር፣ ይህም የሆነበት ምክንያት “እንደ ጌታዬ ቀጥ ብዬ ለመሰቀል የተገባው አይደለሁም” በማለቱ ነው። በሮም የሚገኘው ታላቁ “ባዚሊካ” (ቤተክርስቲያን) በዚሁ የመጀመሪያው የሮም ጳጳስ በነበረው በቅዱስ ጴጥሮስ  መቃብር ላይ የታነጸ ቤተክርስቲያን ነው።

የሮማው አቡን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በመባል የሚታወቁ ሲሆን ትርጓሜውም የመላዋ ቤተክርስቲያን አባት ማለት ነው። የመጀመሪያው የቅዱስ ጴጥሮስ ተከታይ ጳጳስ ሊኖስ ይባላሉ፣ ሁለተኛው ደግሞ አናክሊቱስ የሚባሉ እንደ ነበሩ ከታሪክ የምንረዳ ሲሆን በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ ቄለመንጦስ የሚባሉ ነበሩ። በ180 ዓ.ም. ቅዱስ እረኔዎስ መናፍቃንን በመቃወም በጻፉት መጽሐፍ ውስጥ እስከ ራሳቸው ዘመን ድረስ ቤተክርስቲያንን የመሩዋትን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትን መጥቀሳቸው ከታሪክ መዝገብ ለመረዳት የሚቻል ሲሆን ከዚያም ጊዜ አንስቶ እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ ያሉትን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮን ጨምሮ 266 ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን አስተዳድረዋታል፣ በዚህም ዓይነት ያልተቋረጠ መተካካት ቤተክርስቲያናችን እስከ ዛሬው እለት ዘልቃለች።

ሰለዚህም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ከሮማው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ባላቸው አንድነት የተነሳ ከቅዱስ ጴጥሮስ ዓለት ጋር ያልንን ያልተቋረጠ ግንኙነት ይመሰክራሉ። ስለሆነም መላው የካቶሊክ ማኅበረሰብ የሮማን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በጣም ያውዳሉ ያከብራሉም።

ይህም የካቶሊክ እምነታችን ነው። የሮማው ጳጳስ የቅዱስ ጴጥሮስ ቀጥተኛ ተከታይ ናቸው፣ ስለዚህም “ፓፓ” ወይም የመላይቷ ቤተክርስቲያን አባት እያልን እንጠራቸዋለን። የሮም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ቅዱስ ጴጥሮስ በክርስቶስ አፍ “ዓለት” በተባለው መሠረት የጴጥሮስ “ዓለት” ናቸው። ዋና ተግባራቸውም የቤተክርስቲያኑዋን አንድነት መጠበቅ እና የክርስቶስን መልእክት ከሐሰተኛ መልእክቶች መከላከል ነው።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አይሳሳቱ ብለን እናምናለን

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አይሳሳቱም ማለት ግን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እንደማንኛውም ሰው ኃጢኣት አይሠሩም ማለት ወይም የግል የሆነ ኃጢኣት የላቸውም ማለታችን አይደለም። እንደ ማንኛውም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመን “በእኔ ክፍት በድዬኃለሁን ይቅር በለኝ” እያሉ የግል ኃጢኣታቸውን ይናዘዛሉ።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አይሳሳቱም ስንል በማንኛውም በሚናገሩትና በሚሰሩት ነግሮች ሁሉ አይሳሳቱም ማለታችንም አይደለም። እርሳቸው የማይሳሳቱት ከጴጥሮስ መንበር ላይ ሆነው በይፋ ታላቅ ሃይማኖታዊ አዋጆችን ሲያውጁ፣ ለምሳሌም “ማሪያም በሥጋ እና በነፍስ ወደ ሰማይ የፈለሰችበትን አንቀጸ-ሃይማኖት ወይም ዶግባ ሲያስተላልፉ አይሳሳቱም። እንዲህ ዓይነቱ ታላቅ ሃይማኖታዊ ድንጋጌዎችን “ዶግማ” ወይም አንቀጸ-ሃይማኖት እንላቸዋለን። ካቶሊኮች በሙሉ እንዲህ ዓይነቱን አስተምህሮ እውነት ነው ብለው ይቀበላሉ።

ምንጭ፣-የካቶሊክ እምነታችንን ምንነት፣ የኢትዮጲያ ካቶሊካዊት ጠቅላይ ጽህፈት ቤት ሐዋሪያዊ ሥራዎች ኮሚሽን 2007 .. ካሳተመው መጽሐፍ ከገጽ ግጽ 14, 15 የተወሰደ! የዚህን አስተምህሮ ቀጣይ ክፍል በሚቀጥለው ረዕቡ እናቀርብላችኃለን።

 

 

 


እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያምን የተመለከቱ አራቱ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን አንቀጸ-እምነት በአጭሩ

$
0
0

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያምን የተመለከቱ አራቱ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን

አንቀጸ-እምነት

እንደ አገራችን ሥርዓተ አምልኮና መንፈሳዊ ልማድ በእመቤታችን በኩል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ስለገለጠው ተስፋና በእርስዋም ጸጋ መሞላት ላደረገልን ቸርነት በተለየ ሁኔታ በየዓመቱ ለ16 ቀናት የሚዘለቀወን ጾምና ምህለላ የምናደርግበት የፍልሰታ ዘመን ላይ እንገኛለን። እግዚአብሔር አብ በእርሱ ለኖሩት ሁሉ ሊያደርግላቸው ቃል የገባውን እውነታ እርሱ በፈቀደው መልኩ በእመቤታችን የተገበረበትን ጸጋ እንወድሳለን፤ ለእኛም ይሆንልን ዘንድ “ሰአሊ ለነ ማርያም ኀበ ወልደኪ ኄር መድኃኔ ዓለም” /ማርያም ሆይ! ቸር፣ የሰው ልጆች ሁሉ አዳኝ ወደ ሆነው ልጅሽ ለምኝልን/ በማለት የእናትነት አማላጅነቷን እንማጠናለን።

የካቶሊክ ቤተክርስቲያን እመቤታችን ቅድስት ደንግል ማሪያም በደኅንነት ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ አስትዋጾ በእግዚኣብሔር እንደተሰጣት ታምናለች፣ ታስተምራለችም። በዚሁ ምክንያት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ካላት አክብሮት እና ፍቅር በመነሳት በቤተክርስቲያኗ የእመነት ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት ውስጥ ማሪያምን የተመለከተ 4 ዶግማዎች ወይም አንቀጸ-እምነት የማይሻር የማይለወጥ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ውስጥ እንዲካተቱ አድርጋላች። እነዚህ ማሪያምን የተመለከቱ ዶግማ ወይም ደግሞ የማይሻር የማይለወት አንቀጸ-እምነት የሚባሉት የሚከተሉት ናቸው።

  1. ማሪያም የእግዚኣብሔር እናት ናት

ማሪያም ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ጸንሳ በመውለዱዋ የተነሳ እግዛኢብሔር የሆነው የኢየሱስ እናት በመሆኑዋ የተነሳ “የእግዚኣብሔር እናት ናት” ተብላ ትጠራላች። ይህም ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት (የማይለወጥ የማይሻር የቤተክርስቲያን አስተምህሮ) እንደ አውሮፓዊያን የቀን አቆጣጠር በ431 በተደረገው የኤፌሶን ጉባሄ ከጸደቀ ቡኃላ እስከ ዛሬ ቀን ድረስ ቤተክርስቲያን ይህንን አስተምህሮ በማስተማርና በመጠበቅ ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ያላትን አክብሮት በመግልጽ ላይ ተገኛለች።

2. ማሪያም ለዘለዓለም ድንግል ናት

ማሪያም ኢየሱስን ተፈጥሮአዊ በሆነ መልኩ እኛ በተወለድንበት መንገድ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ጸንሳ በመውለዱዋ የተነሳ ለዘለዓለም ድንግል ሆና ትኖራለች የሚለውና እንደ አውሮፓዊያን የቀን አቆጣጠር በ649 ዓ.ም. በላቴራን ጉባሄ የጸደቀው ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት ነው።

3. ማሪያም ያለ አዳም ኃጢኣት የተጸነሰች ናት

በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ ማሪያም ያለ አዳም ኃጢኣት የተጸነሰች ናት የሚለው ነው። በዚህም በማይለወጥ እና በማይሻር አንቀጸ-እምነት አስተምህሮ ማሪያም ቀደም ሲልም ቢሆን በእግዚኣብሔር የማዳን እቅድ ውስጥ በመኖሩዋ የተነሳ የእርሱ ማለትም የእግዚኣብሔር ልጅ ማደሪይ ትሆን ዘንድ አስቀድሞ ስለመረጣት እኛ ሁላችን ከአዳም የወረስነውንና በጥምቀታችን ቀን ከሚደመሰሰው ኃጢኣት ነጻ ሆና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያ እንድትወለደ እግዚኣብሔር በማድረጉ የተነሳ እመቤታችን “ካለአዳም ኃጢያት ተጸንሳ የተወልደች ነች” የሚለው ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት እንደ የአውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር በ1854 ዓ.ም. በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፒዮ 9ኛ ጸድቆ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት የማይሻር የማይለወጥ አስተምህሮ እንዲሆን ተደርጉዋል።

4. ማሪያም በሥጋ እና በነብስ ወደ ሰማይ ፈልሳለች

በአራተኛ እና በመጨረሻ ደረጃ የምናገኘው ደግሞ ከ6ኛ ክፍለ ዘመን አንስቶ እስከ ዛሬው ቀን ደረስ በምስራቃዊያን የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናትና በካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናትም ጭምር እየተከበረ የሚገኘው ማሪያም በሥጋ እና በነፍስ ወደ ሰማይ ወጣች የሚለውና በአሁኑ ጊዜ እኛ እየጾምነው የምንገኘውን የፍልሰታ ቀን የሚያስታውሰን ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት ምንም እንኳን ከስድስተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እየተከበረ፣ እየተዘከረ የሚገኝ ክብረ በዓል ቢሆንም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት የማይለወጥ የማይሻር አስተምህሮ ተደርጎ በሕግ ውስጥ የሰፈረው ግን እንደ አሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር በ1950 ዓ.ም. በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፒዮስ 12ኛ ከጸደቀ ቡኃላ ነው።  

ኢየሱስ ወደ ዚህ ምድር መቶ ተስቃይቶ ተሰቅሎ መሞቱን እና በሦስተኛው ቀን ከሙታን መነሳቱን በሚዘከርበት የእርገት ቀን መካከል እና ማሪያም ወደ ሰማይ የፈለሰችበት አጋጣሚዎች ግን የተለያዩ እንደ ሆነ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጠንቅቀን እንድንረዳ አደራ ትለናለች። የእግዚኣብሔር ልጅ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣  ሞትን ድል ነስቶ ወደ ሰማይ የወጣው በመለኮታዊ ኃይሉ አማክይነት ሲሆን ነገር ግን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያ ወደ ሰማይ የፈለሰቺው በእግዚኣብሔር መለኮታዊ ኃይል እንደ ሆነ ልብ ሊባል ይገባል።

(አባ መብራቱ ኃይለጊዮርጊስ)

 

 

የፍልሰታ ማሪያም ታሪክ ባጭሩ

$
0
0

ፍልሰታ ማሪያም

እንደ አገራችን ሥርዓተ አምልኮና መንፈሳዊ ልማድ በእመቤታችን በኩል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ስለገለጠው ተስፋና በእርስዋም ጸጋ መሞላት ላደረገልን ቸርነት በተለየ ሁኔታ በየዓመቱ ለ16 ቀናት የሚዘለቀወን ጾምና ምህለላ የምናደርግበት የፍልሰታ ዘመን ላይ እንገኛለን። እግዚአብሔር አብ በእርሱ ለኖሩት ሁሉ ሊያደርግላቸው ቃል የገባውን እውነታ እርሱ በፈቀደው መልኩ በእመቤታችን የተገበረበትን ጸጋ እንወድሳለን፤ ለእኛም ይሆንልን ዘንድ “ሰአሊ ለነ ማርያም ኀበ ወልደኪ ኄር መድኃኔ ዓለም” /ማርያም ሆይ! ቸር፣ የሰው ልጆች ሁሉ አዳኝ ወደ ሆነው ልጅሽ ለምኝልን/ በማለት የእናትነት አማላጅነቷን እንማጠናለን። 
በኢትዮጵያ የሚገኙ በተለይ የምሥራቃዊ ሥርዓተ አምልኮ የሚከተሉ አገረ ስብከቶች ማለትም የአዲስ አበባ፣ የዓዲግራትና የእምድብር አገረ ስብከት ምእመናን በነዚህ ቀናት የሚደረገውን ጾምና ልዩ መንፈሳዊነት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን ምእመናን ጋር የሚጋሩ ሲሆን ከበስተጀርባ ያለውን የአገራችንን ትውፊት አውቀን ይህን ወቅት የመጠቀሙን አስፈላጊነት ስላመንበት ከ http://www.zeorthodox.org/ ድረ ገጽ ያገኘነውንና ከቃሉ ትርጉም በመነሣት ከትውፊትና ከቅዱስ መጽሐፍት በማጣቀስ የፍልሰታ ለማርያምን ትርጉምና መንፈሳዊነት የሚገልጸውን ጽሑፍ ቃል በቃል ከዚህ በታች አስፍረነዋል። 
• ፍልሰታ ማለት ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ማዛወር የነበሩበትን ሀገር ለቆ ወደ ሌላ ሀገር መሰደድ መፍለስ ማለት ነው፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሲባልም የእመቤታችን ሥጋ ከጌቴሰማኒ ወደ ገነት መፍለስን በኋላም በገነት በእፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለማመልከት የሚነገርነው፡፡
• እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 64 ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ በሞት ከተለየች በኋላ እንደ አንድ ልጅዋ ሞታ መነሣቷንና እርገቷን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት ከነሐሴ 1 እስከ 16 የጾሙት ጾም ነው፡፡ ጾመ ፍልሰታ ከሰባቱ አበይት አጽዋማት አንዱ ሆኖ በቀኖና እንዲጾም ከተወሰነበት ጊዜ ጀምሮ ምእመናን ይጾሙታል፡፡
• እመቤታችን በ5485 ዓ.ዓ ከአባቷ ከኢያቄም ከእናቷ ከሐና “እም ሊባኖስ ትወጽእ መርዓት፡፡ ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች” ተብሎ በተነገረው መሠረት ነሐሴ 7 ቀን ተጸነሰች፡፡ ግንቦት አንድ ቀን ሊባኖስ በምትባል ወረዳ በብጽአት እንደተወለደች የቤተክርስቲያን ታሪክ በሰፊው ያስረዳል፡፡ በጾም በጸሎት በአስተብቁዖት የተገኘችናት፡፡ ንጽሕት በመሆኗም ማኅደረ እግዚአብሔር ሆናለች፡፡

እመቤታችን ከእናትና ከአባቷ ዘንድ ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ 12 ዓመት፣ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ 33 ዓመት ከሦስት ወር፣ ከዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ዘንድ 14 ዓመት ከዘጠኝ ወር ጠቅላላ ድምር 64 ዓመት ሲሆናት ጥር 21 ቀን በ49 ዓመተ ምሕረት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡

• ወዳጁን ውበቱን ተነሺ ነይ እያለ የተጣራው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ተጠሪዋም እመቤታችን ናት፡፡ እነሆ ክረምት አለፈ ማለት በስደት በአይሁድ የዘወትር ጠላትነት በልጅዋ መከራና ስቅላት ስምዖን በቤተ መቅደስ እንደተናገረ ልቧ በሀዘን ሠይፍ የተከፈለበት በሀዘን ፍላጻ የተወጋበት የመከራ ክረምት /ወቅት/ አልፎ የክርስቶስ ሕማሙ ፣ ሞቱ፣ ቤዛነቱ ተፈጽሟል፡፡ ትንሣኤው በምድር ላይ ተገልጧል፣ ተሰብኳል ማለት ነው፡፡ በምድራችን አበባ ታይቷል ማለት የሐዋርያት ድምፅ በምድር ሁሉ ደርሷል ማለት ነው፡፡
• የእግዚአብሔር መልአክ የእመቤታችን ሥጋ ከሐዋርያው ዮሐንስ ጋር ተድላ ደስታ ወደ አለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቁ፡፡ ጌታም የእመቤታችንን ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው፡፡ እነርሱም ትወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል አሏት፡፡ ያን ጊዜም ከእፅ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን የማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡ ጌታችንም ዘላለማዊ ወደሆነ መንግሥተ ሰማያት መላእክት እና ሰማእታት እየሰገዱላት አሳረጓት፡፡

• የእመቤታችን ትንሣኤና እርገት መታሰቢያ - በጾመ ፍልሰታ ወቅት ብዙዎች ከቤታቸው ተለይተው በመቃብር ቤት ዘግተው፣ አልጋና ምንጣፍ ትተው፣ በመሬት ላይ ተኝተው ዝግን ጥሬ እፍኝ ውኃ እየቀመሱ በጾምና በጸሎት በመትጋት በታላቅ ተጋድሎ ይሰነብታሉ፡፡ በሰሙነ ፍልሰታ ምእመናን ለእመቤታችን ያላቸውን ጽኑና ጥልቅ ፍቅር የሚያሳዩበት ነው፡፡
• ጌታችን ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር ቆይቶ ሙስና መቃብር ሳያገኘው፣ መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በሥልጣኑ እሑድ በመንፈቀ ሌሊት እንደተነሣ ሁሉ እርሷም በተቀበረች በሦስተኛው ቀን ማኅደረ መለኮት ናትና ሰውነቷ ሳይበሰብስ  መቃብር ሳያገኛት መግነዝ ፍቱልኝ፣ መቃብር ክፈቱልኝ ሳትል የልጅዋ ሥልጣን ኃይል ሆኗት መነሣቷን ትንሣኤዋ “ከመ ትንሣኤ ወልዳ፤ እንደ ልጅዋ ትንሣኤ” ነው ተብሎ ሲከበርላት ይኖራል፡፡
• በዚሁ በነሐሴ 16 ቀን የሰማእቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፍልሰቱ ነው፡፡ ሥጋው ከፋርስ ሀገር ወደ ሀገሩ ወደ ልዳ በክብር የፈለሰበት ነው፡፡ ፍልሰቴን ከፍልሰትሽ አድርጊልኝ፣ ብሎ ለምኗት ስለነበር ፍልሰቱ ከእመቤታችን ፍልሰት ጋር እንዳሰበው ሆኖለታል፡፡ ስለዚህም እርሷን መውደዱ የሚያውቁ ሥእሉን ከሥእሏ አጠገብ ይስላሉ፡፡ በስሙ ለሚማጸኑ የድኅነት ወደብ ይሆን ዘንድ፡፡ 

 

ምንጭ፦ በኢትዮጲያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የሲታዊያን ማኃበር ድህረ ገጺ ከሆነው http://www.ethiocist.org በነሐሴ 6/2009 ዓ.ም. የተወሰደ።

የካቶሊክ እምነታችን ምንነት ክፍል ሁለት

$
0
0

የካቶሊክ እምነታችን ምንነት ክፍል ሁለት

እኛ ካቶሊካዊያን የክርስቶስ መስቀልና የቅዱሳንን ምስሎች እንወዳለን እናከብራለንም

ወደ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ስንገባ ሁል ጊዜ የክርስቶስ ቅዱስ መስቀልና የቅዱሳንን ምስል እናያለን። በቤታችንም ቢሆን የክርስቶስ መስቀልና የቅዱሳን ሰዎች ምስል ወይም ስዕል ማስቀመጥ የተለመደ ነው። ይህንን በማድረጋችን የተነሳ የሚወቅሱንና የሚነቅፉን ሰዎች አሉ። “እናንተ ካቶሊኮች የእንጨት መስቀልና የድንጋይ ሃውልት ታመልካላችሁ” መጽሐፍ ቅዱስ ግን በዘለዋዊያን 26:1 “ትሰግዱላቸው ዘንድ ጣዖታትን አታብጁ፤ ምስል ወይም የማምለኪያ ዐምድ አታቁሙ፤ በምድራችሁም ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) ነኝ” ይላል ይሉናል። ይህን እና ይህንን ለመሳሰሉ ጥያቄዎች በአክብሮት እንዲህ እያልን እንመልሳለን።

እኛ ካቶሊኮች የእኝጨት መስቀል ወይም የድንጋይ ሐውልት ብፍጹም አናመልክም፣ እኛ የምናመልከው እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ያለውን እና ሕያው የሆነውን ክርስቶስን ብቻ ነው። የሆነ ሆኖ በመስቀል ስለ እኛ ተሰቅሎ የሞተውን ጌታችንን የሚያስታውሰን እና እርሱን የበለጠ እንድንወደው የሚረዳን ማስታወሻ እንጂ ማምለኪያ አይደለም።

እስቲ ለአፍታ ይህል በየቤቶችችን የምንሰቅላቸውን የቤተሰቦቻችንን ፎቶ እናስብ። የእነርሱን ፎቶዎች በምንመለከትበት ጊዜ በሕይወት እያሉ ለእኛ የነበራቸውን ፍቅር እና መልካም ሥራ ሁሉ እናስታውሳለን። በተመሳሳይ መልኩ በግርግዳ ላይ የምንሰቅለው የክርስቶስ መስቀል ወይም የእርሱ ምስል ክርስቶስ ለእኛ ያለውን ፍቅርና እርሱ ለእኛ ያደረገውን መልካም ሥራዎች ሁሉ ያስታውሰናል ማለት ነው።

እኛ ካቶሊኮች በዚህ መልኩ የቅዱሳን ምስሎችን፣ ለምሳሌም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማሪያምን፣ የቅዱስ ዮሴፍን፣ የቅድስት ትሬዛን ወዘተርፈ ስዕሎችን ወይም ምሥሎችን በቤታችን ማስቀመጥ እንወዳለን። አሁንም ይህንን የምናደርገው እነዚህን ሰዎች ስለምናመልካቸው ሳይሆን ስለምንወዳቸው ነው። በእምነት ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ስለሆኑ ነው፣ አንድ አንዴም በእምነት ቅድመ አያቶቻችን ናቸው ብለን እንጠራቸዋለን። እነርሱም መልካም አረአያዎቻችን ናቸው። ታዲያ የእነዚህን ሰዎች ምስል በቤታችን ብናስቀምጥ ምን ችግር አለው? በአጭሩ እኛ ካቶሊኮች ሞትን ድል አድርጎ ከሙታን የተነሳውን ከክርስቶስ በቀር ማንንም አናመልክም።

የእንጨት መስቀል ለእኛ ሲል በመስቀል ተሰቅሎ የሞተውን ክርስቶስን የሚያስታውሰን ማስታወሻ ነው። ክርስቶስን የበለጠ እንድነወደውና በእየለቱም መስቀሎቻችንን ከእርሱ ጋር ሆነን በመሸከም ክርስቲያናዊ ጉዞዎችንን በጽናት እንድጓዝ ያደርገናል።

በተጨማሪም የቅዱሳን ሰዎች ምስል ልክ የቤተሰብ የፎቶ ማስቀመጫ አልበም ቤተሰቦቻችንን እንደ ሚያስታውሰን በእመነት ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የሆኑ ሰዎች ከነሥራቸው የሚያስታውሰን ነው። በተጨማሪም ክርስቶስን እነርሱ በተከተሉት መንገድ እንድንከተለው ያበረታቱናልና በዚሁ ምክንያት እኛም ካቶሊኮች የቅዱሳን ሰዎችን ምስል በቤታችን ማስቀመጥ የምንወደው።

መጽሐፍ ቅዱስ እና ምስሎች ምን ይላል!

መጽሐፍ ቅዱስ በኢየሩሳሌም ቤተ መቅድስ ውስጥ ስለነበረው ከእጨት ስለተሠራው ምስልና ሙሴ በእግዚኣብሔር ትዕዛዝ ሠርቶት በበረሃ ስለሰቀለው የነሐስ እባብ ይናገራል። በአንደኛው መጽሐፈ ነገሥት 6:23-28 እንዲህ የሚል ነገር እናገንእለኝ። “የእያንዳዳቸው ቁመት አራት  ሜትር ከአርባ ሳንቲ ሜትር የሆነ ከወይራ እንጨት በሁለት ኪሩቤል አምሳል የተቀረጹ ምስሎችን በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ሠራ” ይላል።

ንጉሥ ሰለሞንና ሕዝቡ እነዚህን ምስሎች አላመለኩዋቸውም፣ ነገር ግን እነዚህ ምስሎች በጊዜው የነበሩትን ሰዎች ሁሉ በመላእክት ተከበበው በእግዚኣብሔር ጥበቃ ሥር እናድሉ እግዚኣብሔርም ከእነርሱ ጋር እዳለ እንዲረዱ፣ ያ ስሜት በውስጣቸው እንዲፈጠር ረድቷቸዋል። 

ከዚህ በላይ በተጠቀሰው ምክንያት ነው እኛ ካቶሊኮች የእንጨት ምስሎችንና ሥዕሎችን ይምንሠራው፣ መስቀል ስናይ ከሙታን የተነሳው ክርስቶስ ስለእኛ የተሰቀለው እና የሞተው ክርስቶስ አሁንም በመካከላችን እንዳለ ይሰማናል። የቅዱሳን ሰዎች ምስልም እነርሱ ክርስቶስን በተከተሉበት የቅድስና መንገድ እንድንከተል ያነሳሳናል።  

ምንጭ፣-የካቶሊክ እምነታችንን ምንነት፣ የኢትዮጲያ ካቶሊካዊት ጠቅላይ ጽህፈት ቤት ሐዋሪያዊ ሥራዎች ኮሚሽን በ2007 ዓ.ም. ካሳተመው መጽሐፍ ከገጽ ግጽ 20, 21 የተወሰደ! የዚህን አስተምህሮ ቀጣይ ክፍል በሚቀጥለው ረዕቡ እናቀርብላችኃለን።

 

የፍልሰታ ማሪያም አስተምህሮ ክፍል ሦስት

$
0
0

የፍልሰታ ማሪያም አስተምህሮ ክፍል ሦስት

እንደ አገራችን ሥርዓተ አምልኮና መንፈሳዊ ልማድ በእመቤታችን በኩል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ስለገለጠው ተስፋና በእርስዋም ጸጋ መሞላት ላደረገልን ቸርነት በተለየ ሁኔታ በየዓመቱ ለ16 ቀናት የሚዘለቀወን ጾምና ምህለላ የምናደርግበት የፍልሰታ ዘመን ላይ እንገኛለን። እግዚአብሔር አብ በእርሱ ለኖሩት ሁሉ ሊያደርግላቸው ቃል የገባውን እውነታ እርሱ በፈቀደው መልኩ በእመቤታችን የተገበረበትን ጸጋ እንወድሳለን፤ ለእኛም ይሆንልን ዘንድ “ማርያም ሆይ! ቸር፣ የሰው ልጆች ሁሉ አዳኝ ወደ ሆነው ልጅሽ ለምኝልን/ በማለት የእናትነት አማላጅነቷን የምንማጽንበት የፍልሰታ ወቅት ላይ እንገኛለን።

ከ6ኛ ክፍለ ዘመን አንስቶ እስከ ዛሬው ቀን ደረስ በምስራቃዊያን የኦርቶዶክ አብያተ ክርስቲያናትና በካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናትም ጭምር እየተከበረ የሚገኘው ማሪያም በሥጋ እና በነፍስ ወደ ሰማይ ወጣች የሚለውና በአሁኑ ጊዜ እኛ እየጾምነው የምንገኘውን የፍልሰታ ወቅት ምንም እንኳን ከስድስተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ እየተከበረና እየተዘከረ የሚገኝ ክብረ በዓል ቢሆንም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ዶግማ ወይም አንቀጸ-ሐይማኖት የማይለወጥ የማይሻር አስተምህሮ ተደርጎ በቤተክርስቲያኗ ሕግጋት ውስጥ የሰፈረው ግን እንደ አሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር በ1950 ዓ.ም. በወቅቱ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነበሩት ፒዮስ 12ኛ ከጸደቀ ቡኃላ ነው።

እንደ አውሮፓውያኑኑ የቀን አቆጣጠር በኅዳር 1/1950 ዓ.ም. ላይ በወቅቱ ያካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቃነ ጳጳሳት የነበሩት ፒዮስ 12ኛ ማሪያም ምድራዊ ሕይወቷ ሲያበቃ በነብስ እና በሥጋ ወደ ሰማይ ፍልሳለች የሚለውን አስተምህሮ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ዶግማ ወይም አንቀጸ-ሐይማኖት የማይሻር የማይለወጥ አስተምህሮ እንዲሆን በደነገጉበት ወቅት ይህን አንቀጸ-እምነት በሚገባ በሚያብራራው በላቲን ቋንቋ ሙኒቼንቲሲሙስ ዴውስ በአማሪኛው በግድፉ ሲተረጎም እጹብ ድንቅ እግዚኣብሔር በተሰኘው ሐዋሪያዊ ሕግ-ጋት ላይ በቁጥር አንድ እስከ አምስት ያለውን ማሪያም ምድራዊ ሕይወቷ ሲያበቃ በነብስ እና በሥጋ ወደ ሰማይ ፍልሳለች የሚለውን አስተምህሮ በሚከተለው መልኩ ያብራራሉ።

1. እጅግ የተትረፈረፈ እና ሁሉን ቻይ የሆነው እግዚአብሄር በጥበብና በፍቅር ላይ በማትኮር፣ በእራሱ ምስጢራዊ ዓላማ በሐዘን ውስጥ የሚገኙትን የሕዝቦቹን እና ግለሰቦችን በሕይወታቸው ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ደስታን በማኖር በተለያየ ሁኔታ እና በተለያየ መንገድ በመሥራት ለሚወዱት ሰዎች ነገሮች በመልካም ሁኔታ እንዲከናወኑ ያደርጋል” ይለናል።

2. እምቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም በክርስቶስ ደም በዳኑ ሰዎች ሁሉ ስም በመሆን የእናትነት ኃልፊነቷን በሚገባና ብቃት ባለው መልኩ በመወጣቷ የተነሳ የእርሷ ልጆች የሆንን የእኛ ልብ እና ሕሊናችን ሳይቀር ወደ እርሱ እንዲሳብ ማድረግ ችላለች።

3. እግዚኣብሔር የመረጠው እና የፈቀደ ጊዜ በደረሰ ጊዜ እርሱ በመረጣት እና በወደዳት እምቤታችን ማሪያም ላይ የመንፈስ ቅዱሱን ጥበቃ በማወረድ ምልአት ባለው መልኩ ከሴቶች ሁሉ በመምረጥ ፍጹም በሆነ ጸጋ የተሞላ ጥምረት ፈጠሩን የካቶሊክ ቤተክርስቲያን በግልጽ የምትስተምረው እውነታ ነው።

4. ለዚህም ነው እንግዲህ ቤተክርስቲያናችን በየክፍለ ዘመናቱ ይህንን የተመለከቱ ተከታታይ ጥናቶችን በማድረግ አሁንም ቢሆን ማሪያም በሥጋና በነፍስ ወደ ሰማይ እንደ ፈለሰች በማስተማር እና ይህንንም እምነት አጥብቃ በመጠበቅ የእጊግዚኣብሔር እናት የሆነችው ቅድስት ድንግል ማሪያ ሁሌም ደምቃ ትታይ ዘንድ የምትጥረው።

ከዚህ ቀደም እንደ አውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር 1854 በወቅቱ የነበሩት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በፒዮስ 9ኛ ማሪያም ያለ አዳም ኃጢኣት የተጸነሰች ናት የሚለውን ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት የማይሻር የማይለወጥ አስተምህሮ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሕግ ጋት ውስጥ እንዲካተት በማድረጋቸው የተነሳ ለማሪያም ያለው ክብር ከፍ እንዲል አድርጎታል።

ክርስቶስ በሞቱ ኃጢኣትን እና ሞትን ድል አድርጉዋል፣ ሰለዚህም በጥምቀት እንደገና የተወለዱ ሁሉ መለኮታዊ በሆነ ኃይል በክርስቶስ አማክይነት ሞትን ድል ያደርጋሉ። ነገር ግን እግዚኣብሔር የዓለም ፍጻሜ እስኪ መጣ ድረስ ሞትን ድል የመሳት ስጦታ ሙሉ በሙሉ ገቢራዊ እንዲሆን አላደረገም። ለዚህም ነው ታዲያ በጣም መልካም የሚባሉ ሰዎች ሥጋ ሳይቀር ከሞቱ ቡኃላ በድናቸው በመጨረሻው ቀን ከሙታን መነሳት በሚመጣበት ወቅት ነብሳቸው እና ሥጋቸው በታላቅ ክብር እስኪዋሃዱ ድረስ እንዲበሰብስ የሚያደርገው።

ነገር ግን እግዚኣብሔር ይህንን አጠቃላይ የሆነ ሕግ በማሪያም ላይ አልተገበረውም። እርሷ እግዚኣብሔር በሰጣት ልዩ መብት የተነሳ ከአዳም የወረስነው ኃጢኣያት ሳይነካት እንድትጸነስ በማድረጉ ኃጢኣያት እንዲነካት አላደረገም፣ በዚህም ሰበብ ሥጋዋ እንደማንኛውም ሰው በመቃብር ውስጥ እንዲበሰብስ በለመደረጉ የተነሳ ነው እንግዲህ እኛ ሁላችን እስከ መጨረሻው ቀን ድረስ መጠበቅ የሚገባንን የነብስ እና የሥጋ ትንሣኤ እርሷ እስከ መጨረሻው ቀን ድረስ መጠበቅ ያልተገደደችሁ በዚሁ ምክንያት ነው።

ኢየሱስ ወደ እዚህ ምድር መቶ ተስቃይቶ ተሰቅሎ መሞቱን እና በሦስተኛው ቀን ከሙታን መነሳቱን በሚዘከርበት የእርገት ቀን መካከል እና ማሪያም ወደ ሰማይ የፈለሰችበት አጋጣሚዎች ግን የተለያዩ ሁኔታዎች እንደ ሆኑ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጠንቅቀን እንድንረዳ አደራ ትለናለች። የእግዚኣብሔር ልጅ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣  ሞትን ድል ነስቶ ወደ ሰማይ የወጣው በመለኮታዊ ኃይሉ አማክይነት ሲሆን ነገር ግን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያ ወደ ሰማይ የፈለሰቺው በእግዚኣብሔር መለኮታዊ ኃይል እንደ ሆነ ልብ ሊባል ይገባል።

የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ በቁጥር 966 ላይ “በመጨረሻም ንጽሕት ድንግል ማሪያም ከአዳም ኃጢኣት ሁሉ ተጠብቃ የምድራዊ የሕይወቷ ጉዞ ሲያበቃ በነብስ እና በሥጋ ወደ ሰማያዊ ክብር ተወሰደች። የጌቶች ሁሉ ጌታ ከሆነውና ኃጢኣትንና ሞትን ካሸነፈው ከልጇ ጋር አንድነቷ ይበልጥ የተሟላ መሆንኑን ለመመስከር በሁሉም ነገሮች ላይ ንግሥት ሆና በጌታ ከበረች”።  የብፅዕት ድንግል እርገት በልጇ ትንሣኤ ያደረገችሁ ልዩ ተሳትፎ ከመሆኑም በላይ የሌሎች ክርስቲያኖች ተስፋ ነው” በማለት ቀደም ሲል የተጠቀሰውን ማብራሪያ ያጠናክራል።

 

 

 

የፍልሰታ ማሪያም አስተምህሮ ክፍል አራት

$
0
0

የፍልሰተ ማሪያም አስተምህሮ ክፍል አራት

እንደ አገራችን ሥርዓተ አምልኮና መንፈሳዊ ልማድ በእመቤታችን በኩል እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ስለገለጠው ተስፋና በእርስዋም ጸጋ መሞላት ላደረገልን ቸርነት በተለየ ሁኔታ በየዓመቱ ለ16 ቀናት የሚዘለቀወን ጾምና ምህለላ የምናደርግበት የፍልሰታ ዘመን ላይ እንገኛለን። እግዚአብሔር አብ በእርሱ ለኖሩት ሁሉ ሊያደርግላቸው ቃል የገባውን እውነታ እርሱ በፈቀደው መልኩ በእመቤታችን የተገበረበትን ጸጋ እንወድሳለን፤ ለእኛም ይሆንልን ዘንድ “ማርያም ሆይ! ቸር፣ የሰው ልጆች ሁሉ አዳኝ ወደ ሆነው ልጅሽ ለምኝልን/ በማለት የእናትነት አማላጅነቷን የምንማጽንበት የፍልሰታ ወቅት ላይ እንገኛለን።

ኢየሱስ ወደ ዚህ ምድር መቶ ተስቃይቶ ተሰቅሎ መሞቱን እና በሦስተኛው ቀን ከሙታን መነሳቱን በሚዘከርበት የእርገት ቀን መካከል እና ማሪያም ወደ ሰማይ የፈለሰችበት አጋጣሚዎች ግን የተለያዩ እንደ ሆነ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጠንቅቀን እንድንረዳ አደራ ትለናለች። የእግዚኣብሔር ልጅ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣  ሞትን ድል ነስቶ ወደ ሰማይ የወጣው በመለኮታዊ ኃይሉ አማክይነት ሲሆን ነገር ግን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያ ወደ ሰማይ የፈለሰቺው በእግዚኣብሔር መለኮታዊ ኃይል እንደ ሆነ ልብ ሊባል ይገባል።

የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ በቁጥር 966 ላይ “በመጨረሻም ንጽሕት ድንግል ማሪያም ከአዳም ኃጢያት ሁሉ ተጠብቃ የምድራዊ የሕይወቷ ጉዞ ሲያበቃ በነብስ እና በስጋ ወደ ሰማያዊ ክብር ተወሰደች። የጌቶች ሁሉ ጌታ ከሆነውና ኃጢኣትንና ሞትን ካሸነፈው ከልጇ ጋር አንድነቷ ይበልጥ የተሟላ መሆንኑን ለመመስከር በሁሉም ነገሮች ላይ ንግሥት ሆና በጌታ ከበረች”።  የብፅዕት ድንግል እርገት በልጇ ትንሣኤ ያደረገችሁ ልዩ ተሳትፎ ከመሆኑም በላይ የሌሎች ክርስቲያኖች ተስፋ ነው” ይላል።

የእግዚኣብሔር እናት የሆነችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ከመጀመሪያው ማለትም ከጽነሰቷ እለት ጀምሮ ያለ አዳም ኃጢኣያት የተጸነሰች ናት የሚለው አስተምህሮ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ዶግማ ወይም አንቀጸ-እምነት የማይለወጥ የማይሻር አስተምህሮ ተደርጎ በወቅቱ በነበሩት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በፒዮስ 9ኛ እንደ አውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር 1854 ዓ.ም። በተወሰነበት ወቅት በወቅቱ የነበሩ ምዕመናን ልብ በደስታ ተሞልቶ እንደ ነበረና ከዚያም በመቀጠል ማሪያም በሥጋና በነፍስ ወደ ሰማይ መፍለሱዋም በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ውስጥ ይካተታል የሚል ተስፋ አድሮባቸው ነበር።

ለቁጥር የሚያዳግቱ በጣም ብዙ የሚባሉ በዓለም ውስጥ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት መጠሪያቸውን ከማሪያም ስም ጋር በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የተያያዘ ነው። በሚልዮን የሚቆጠሩ ምዕመናን የማሪያምን ሥም በእየለቱ በመጥራት አማላጅነቷን ይማጸናሉ። በሚልዮን የሚቆጠሩ የማሪያም ምስል የያዙ ቅርጻቅርሶች በእየቤቱ በእየቤተክርስቲያኑ በእየሰው አንገትም ላይ ሳይቀር ተሰቅለው ወይም ተንጠልጥለው ማየት የተለመደ ነው።

በካቶሊክ ቤተክርስቲያን እምነት እና ባሕል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያ ከፍተኛ የሆነ ቦታ ተሰጥቱዋት ገዳማት፣ አብያተ ክርስቲያናት ሳይቀሩ በስሟ ተገንብቶላት ከፍተኛ ክብር እየሚሰጣት የቤተክርስቲያን እናት ናት፣ አማላጅነቷንም ሁል ጊዜ እንማጸናለን። የእመበታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም አካባሪ የነበረውና ማሪያም በሥጋ እና በነብስ ወደ ሰማይ ፈልሳለች የሚለው አስተምህሮ እውነት እና ትክክለኛ አስተምህሮ ነው የሚል ጽኑ አቋም የነበረው የደማቆው ቅዱስ ዩሐንስ ስለማሪያም መፍለስ እንዲህ ብሎት ተናግሮ ነበር “ከወለደችም ቡኃላ ድንግልናዋን ጠብቃ የቆየች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ከሞተችም ቡኃላ እንኳን ሰውነቷ ሊበስበስ አይገባውም” ይለናል።

“የፈጣሪን ልጅ የተሸከመች፣ ከጡቷም ያጥባችሁ እናት በመለኮታዊ ድንኳን ውስጥ ለዘለዓለም ልትኖር ይገባታል።  እግዚኣብሔር ለልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ የመረጣት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም በመለኮታዊ ሥፍራ ልትኖር ይገባታል። ልጇን በመስቀል ላይ ያየች እና ልጇን በመለደችበት ወቅት ያየቺውን ስቃይ በማስታወስ የጭንቀት ሰይፍ ልቡዋን የወጋት እናታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም፣ አሁን ደግሞ ከአባቱ ጋር ሲቀመጥ እሱን ማየት ይኖርባታል። የአምላክ እናት የልጇን ውርስ ልትወርስ ይገባታል፣ እንዲሁም  እናትና የአምላክ ድንቅ ሥራ ውጤት በመሆኑ የተነሳ  በፍጥረታት ሁሉ ዘንድ ልትከበር ይገባታል።” በማለት የደማቆው ቅዱስ ዩሐንስ ለማሪያም ያለውን ክብር በመግለጽ በሥጋ እና በነፍስ ወደ ሰማይ መፍለሷን በማመን ያመነውንም በማስተማር እውነታውን ያጠናክራል።

Viewing all 1660 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>